አማርኛ Muhammad Sadiq & Sani Habib
Surah አል አሹዐራዕ - Aya count 227
طسم
( 1 ) 
ጠ.ሰ.መ. (ጧ ሲን ሚም)፡፡

تِلْكَ آيَاتُ الْكِتَابِ الْمُبِينِ
( 2 ) 
ይህች ግልጽ ከኾነው መጽሐፍ አንቀጾች ናት፡፡

لَعَلَّكَ بَاخِعٌ نَّفْسَكَ أَلَّا يَكُونُوا مُؤْمِنِينَ
( 3 ) 
አማኞች ባለመኾናቸው፤ (በቁጭት) ነፍስህን ገዳይ መኾን ይፈራልሃል፡፡

إِن نَّشَأْ نُنَزِّلْ عَلَيْهِم مِّنَ السَّمَاءِ آيَةً فَظَلَّتْ أَعْنَاقُهُمْ لَهَا خَاضِعِينَ
( 4 ) 
ብንሻ በእነሱ ላይ ከሰማይ ተዓምረን እናወርድና አንገቶቻቸው (መሪዎቻቸው) ለእርሷ ተዋራጆች ይኾናሉ፡፡

وَمَا يَأْتِيهِم مِّن ذِكْرٍ مِّنَ الرَّحْمَٰنِ مُحْدَثٍ إِلَّا كَانُوا عَنْهُ مُعْرِضِينَ
( 5 ) 
ከአልረሕማንም ዘንድ ኣዲስ የተወረደ ቁርኣን አይመጣላቸውም፤ ከእርሱ የሚሸሹ ቢኾኑ እንጂ፡፡

فَقَدْ كَذَّبُوا فَسَيَأْتِيهِمْ أَنبَاءُ مَا كَانُوا بِهِ يَسْتَهْزِئُونَ
( 6 ) 
በእርግጥም አስተባበሉ፡፡ የዚያም በእርሱ ይሳለቁበት የነበሩት ወሬዎች (ፍጻሜ) ይመጣባቸዋል፡፡

أَوَلَمْ يَرَوْا إِلَى الْأَرْضِ كَمْ أَنبَتْنَا فِيهَا مِن كُلِّ زَوْجٍ كَرِيمٍ
( 7 ) 
ወደ ምድርም በውስጧ ከመልካም (በቃይ) ጎሳ ሁሉ ብዙን እንዳበቀልን አላዩምን፡፡

إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَآيَةً ۖ وَمَا كَانَ أَكْثَرُهُم مُّؤْمِنِينَ
( 8 ) 
በዚህ አስደናቂ ምልክት አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም አማኞች አልነበሩም፡፡

وَإِنَّ رَبَّكَ لَهُوَ الْعَزِيزُ الرَّحِيمُ
( 9 ) 
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊ አዛኝ ነው፡፡

وَإِذْ نَادَىٰ رَبُّكَ مُوسَىٰ أَنِ ائْتِ الْقَوْمَ الظَّالِمِينَ
( 10 ) 
ጌታህም ሙሳን «ወደ በደለኞቹ ሕዝቦች ኺድ» በማለት በጠራው ጊዜ (አስታውስ)፡፡

قَوْمَ فِرْعَوْنَ ۚ أَلَا يَتَّقُونَ
( 11 ) 
«ወደ ፈርዖን ሕዝቦች (ኺድ) አላህን አይፈሩምን» (አለው)፡፡

قَالَ رَبِّ إِنِّي أَخَافُ أَن يُكَذِّبُونِ
( 12 ) 
(ሙሳም) አለ «ጌታዬ ሆይ! እኔ ሊያስተባብሉኝ እፈራለሁ፡፡

وَيَضِيقُ صَدْرِي وَلَا يَنطَلِقُ لِسَانِي فَأَرْسِلْ إِلَىٰ هَارُونَ
( 13 ) 
«ልቤም ይጠብባል፡፡ ምላሴም አይፈታም፡፡ ስለዚህ ወደ ሃሩን ላክ፡፡

وَلَهُمْ عَلَيَّ ذَنبٌ فَأَخَافُ أَن يَقْتُلُونِ
( 14 ) 
«ለእነርሱም በእኔ ላይ (የደም) ወንጀል አልለ፡፡ ስለዚህ እንዳይገድሉኝ እፈራለሁ፡፡»

قَالَ كَلَّا ۖ فَاذْهَبَا بِآيَاتِنَا ۖ إِنَّا مَعَكُم مُّسْتَمِعُونَ
( 15 ) 
(አላህ) አለ «ተው! (አይነኩህም)፡፡ በተዓምራቶቻችንም ኺዱ፡፡ እኛ ከእናንተ ጋር ሰሚዎች ነንና፡፡

فَأْتِيَا فِرْعَوْنَ فَقُولَا إِنَّا رَسُولُ رَبِّ الْعَالَمِينَ
( 16 ) 
«ወደ ፈርዖንም ኺዱ፡፡ በሉትም፡- እኛ የዓለማት ጌታ መልክተኞች ነን፡፡

أَنْ أَرْسِلْ مَعَنَا بَنِي إِسْرَائِيلَ
( 17 ) 
«የእስራኤልን ልጆች ከእኛ ጋር ልቀቅ፡፡»

قَالَ أَلَمْ نُرَبِّكَ فِينَا وَلِيدًا وَلَبِثْتَ فِينَا مِنْ عُمُرِكَ سِنِينَ
( 18 ) 
(ፈርዖንም) አለ «ልጅ ኾነህ በእኛ ውስጥ አላሳደግንህምን በእኛ ውስጥም ከዕድሜህ ብዙ ዓመታትን አልተቀመጥክምን

وَفَعَلْتَ فَعْلَتَكَ الَّتِي فَعَلْتَ وَأَنتَ مِنَ الْكَافِرِينَ
( 19 ) 
«ያችንም የሠራሃትን ሥራህን አልሠራህምን አንተም ከውለታ ቢሶቹ ነህ» (አለ)፡፡

قَالَ فَعَلْتُهَا إِذًا وَأَنَا مِنَ الضَّالِّينَ
( 20 ) 
(ሙሳም) አለ «ያን ጊዜ እኔም ከተሳሳቱት ኾኜ ሠራኋት፡፡

فَفَرَرْتُ مِنكُمْ لَمَّا خِفْتُكُمْ فَوَهَبَ لِي رَبِّي حُكْمًا وَجَعَلَنِي مِنَ الْمُرْسَلِينَ
( 21 ) 
«በፈራኋችሁም ጊዜ ከእንናተ ሸሸሁ፡፡ ጌታየም ለእኔ ጥበብን ሰጠኝ፡፡ ከመልክተኞቹም አደረገኝ፡፡

وَتِلْكَ نِعْمَةٌ تَمُنُّهَا عَلَيَّ أَنْ عَبَّدتَّ بَنِي إِسْرَائِيلَ
( 22 ) 
«ይህችም የእስራኤልን ልጆች ባሪያ በማድረግህ በእኔ ላይ የምትመጻደቅባት ጸጋ ነት፡፡»

قَالَ فِرْعَوْنُ وَمَا رَبُّ الْعَالَمِينَ
( 23 ) 
ፈርዖን አለ «(ላከኝ የምትለው) የዓለማትም ጌታ ምንድነው»

قَالَ رَبُّ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ وَمَا بَيْنَهُمَا ۖ إِن كُنتُم مُّوقِنِينَ
( 24 ) 
(ሙሳ) «የሰማያትና የምድር በመካከላቸውም ያለው ሁሉ ጌታ ነው፡፡ የምታረጋግጡ ብትኾኑ (ነገሩ ይህ ነው)፤» አለው፡፡

قَالَ لِمَنْ حَوْلَهُ أَلَا تَسْتَمِعُونَ
( 25 ) 
(ፈርዖንም) በዙሪያው ላሉት ሰዎች «አትሰሙምን» አለ፡፡

قَالَ رَبُّكُمْ وَرَبُّ آبَائِكُمُ الْأَوَّلِينَ
( 26 ) 
(ሙሳ) «ጌታችሁና የመጀመሪያዎቹ አባቶቻችሁም ጌታ ነው» አለው፡፡

قَالَ إِنَّ رَسُولَكُمُ الَّذِي أُرْسِلَ إِلَيْكُمْ لَمَجْنُونٌ
( 27 ) 
(ፈርዖን) «ያ ወደእናንተ የተላከው መልክተኛችሁ በእርግጥ ዕብድ ነው» አለ፡፡

قَالَ رَبُّ الْمَشْرِقِ وَالْمَغْرِبِ وَمَا بَيْنَهُمَا ۖ إِن كُنتُمْ تَعْقِلُونَ
( 28 ) 
(ሙሳ) «የምሥራቅና የምዕራብ በመካከላቸውም ያለው ነገር ሁሉ ጌታ ነው፡፡ ታውቁ እንደኾናችሁ (እመኑበት)» አለው፡፡

قَالَ لَئِنِ اتَّخَذْتَ إِلَٰهًا غَيْرِي لَأَجْعَلَنَّكَ مِنَ الْمَسْجُونِينَ
( 29 ) 
(ፈርዖን) «ከእኔ ሌላ አምላክን ብትይዝ በውነቱ ከእስረኞቹ አደርግሃለሁ» አለ፡፡

قَالَ أَوَلَوْ جِئْتُكَ بِشَيْءٍ مُّبِينٍ
( 30 ) 
(ሙሳ) «በግልጽ አስረጅ ብመጣህም እንኳ» አለው፡፡

قَالَ فَأْتِ بِهِ إِن كُنتَ مِنَ الصَّادِقِينَ
( 31 ) 
«እንግዲያውስ ከእውነተኞች እንደኾንክ (አስረጁን) አምጣው» አለ፡፡

فَأَلْقَىٰ عَصَاهُ فَإِذَا هِيَ ثُعْبَانٌ مُّبِينٌ
( 32 ) 
በትሩንም ጣለ፡፡ እርሷም ወዲያውኑ ግልጽ እባብ ኾነች፡፡

وَنَزَعَ يَدَهُ فَإِذَا هِيَ بَيْضَاءُ لِلنَّاظِرِينَ
( 33 ) 
እጁንም አወጣ፡፡ ወዲያውም እርሷ ለተመልካቾች (የምታበራ) ነጭ ኾነች፡፡

قَالَ لِلْمَلَإِ حَوْلَهُ إِنَّ هَٰذَا لَسَاحِرٌ عَلِيمٌ
( 34 ) 
(ፈርዖን) በዙሪያው ላሉት መማክርት «ይህ በእርግጥ ዐዋቂ ድግምተኛ ነው» አለ፡፡

يُرِيدُ أَن يُخْرِجَكُم مِّنْ أَرْضِكُم بِسِحْرِهِ فَمَاذَا تَأْمُرُونَ
( 35 ) 
«ከምድራችሁ በድግምቱ ሊያወጣችሁ ይፈልጋልና ምንን ታዛላችሁ» (አላቸው)፡፡

قَالُوا أَرْجِهْ وَأَخَاهُ وَابْعَثْ فِي الْمَدَائِنِ حَاشِرِينَ
( 36 ) 
አሉት «እርሱን ወንድሙንም አቆይና በየከተሞቹ ሰብሳቢዎችን ላክ፡፡

يَأْتُوكَ بِكُلِّ سَحَّارٍ عَلِيمٍ
( 37 ) 
«በጣም ዐዋቂ ድግምተኞችን ሁሉ ያመጡልሃልና፡፡»

فَجُمِعَ السَّحَرَةُ لِمِيقَاتِ يَوْمٍ مَّعْلُومٍ
( 38 ) 
ድግምተኞቹም በታወቀ ቀን ቀጠሮ ተሰበሰቡ፡፡

وَقِيلَ لِلنَّاسِ هَلْ أَنتُم مُّجْتَمِعُونَ
( 39 ) 
ለሰዎቹም «እናንተ ተሰብስባችኋልን» ተባለ፡፡

لَعَلَّنَا نَتَّبِعُ السَّحَرَةَ إِن كَانُوا هُمُ الْغَالِبِينَ
( 40 ) 
«ድግምተኞቹን እነሱ አሸናፊዎች ቢኾኑ እንከተል ዘንድ» (ተባለ)፡፡

فَلَمَّا جَاءَ السَّحَرَةُ قَالُوا لِفِرْعَوْنَ أَئِنَّ لَنَا لَأَجْرًا إِن كُنَّا نَحْنُ الْغَالِبِينَ
( 41 ) 
«ድግምተኞቹም በመጡ ጊዜ ለፈርዖን እኛ አሸናፊዎች ብንሆን ለእኛ በእርግጥ ዋጋ አለን» አሉት፡፡

قَالَ نَعَمْ وَإِنَّكُمْ إِذًا لَّمِنَ الْمُقَرَّبِينَ
( 42 ) 
«አዎን፤ እናንተም ያን ጊዜ ከባለሟሎቹ ትኾናላችሁ» አላቸው፡፡

قَالَ لَهُم مُّوسَىٰ أَلْقُوا مَا أَنتُم مُّلْقُونَ
( 43 ) 
ሙሳ «ለእነርሱ እናንተ የምትጥሉትን ጣሉ» አላቸው፡፡

فَأَلْقَوْا حِبَالَهُمْ وَعِصِيَّهُمْ وَقَالُوا بِعِزَّةِ فِرْعَوْنَ إِنَّا لَنَحْنُ الْغَالِبُونَ
( 44 ) 
ገመዶቻቸውንና በትሮቻቸውንም ጣሉ፡፡ «በፈርዖንም ክብር ይኹንብን፡፡ እኛ በእርግጥ አሸናፊዎቹ እኛ ነን» አሉ፡፡

فَأَلْقَىٰ مُوسَىٰ عَصَاهُ فَإِذَا هِيَ تَلْقَفُ مَا يَأْفِكُونَ
( 45 ) 
ሙሳም በትሩን ጣለ፡፡ ወዲያውም እርሷ የሚያስመስሉትን ሁሉ ትውጣለች፡፡

فَأُلْقِيَ السَّحَرَةُ سَاجِدِينَ
( 46 ) 
ድግምተኞቹም ሰጋጆች ኾነው ወደቁ፡፡

قَالُوا آمَنَّا بِرَبِّ الْعَالَمِينَ
( 47 ) 
(እነሱም) አሉ «በዓለማት ጌታ አመንን፡፡

رَبِّ مُوسَىٰ وَهَارُونَ
( 48 ) 
«በሙሳና በሃሩን ጌታ፡፡»

قَالَ آمَنتُمْ لَهُ قَبْلَ أَنْ آذَنَ لَكُمْ ۖ إِنَّهُ لَكَبِيرُكُمُ الَّذِي عَلَّمَكُمُ السِّحْرَ فَلَسَوْفَ تَعْلَمُونَ ۚ لَأُقَطِّعَنَّ أَيْدِيَكُمْ وَأَرْجُلَكُم مِّنْ خِلَافٍ وَلَأُصَلِّبَنَّكُمْ أَجْمَعِينَ
( 49 ) 
(ፈርዖንም) «ለእናንተ ሳልፈቅድላችሁ በፊት ለእርሱ አመናችሁን እርሱ ያ ድግምትን ያስተማራችሁ ታላቃችሁ ነው፡፡ ወደፊትም (የሚያገኛችሁን) በእርግጥ ታውቃላችሁ፡፡ እጆቻችሁንና እግሮቻችሁን (ቀኝና ግራን) በማናጋት እቆረርጣለሁ፡፡ ሁላችሁንም እሰቅላችኋለሁም» አለ፡፡

قَالُوا لَا ضَيْرَ ۖ إِنَّا إِلَىٰ رَبِّنَا مُنقَلِبُونَ
( 50 ) 
(እነርሱም) አሉ «ጉዳት የለብንም፡፡ እኛ ወደ ጌታችን ተመላሾች ነን፡፡

إِنَّا نَطْمَعُ أَن يَغْفِرَ لَنَا رَبُّنَا خَطَايَانَا أَن كُنَّا أَوَّلَ الْمُؤْمِنِينَ
( 51 ) 
«እኛ የምእምናን መጀመሪያ በመኾናችን ጌታችን ኀጢአቶቻችንን ለእኛ ሊምር እንከጅላለን፡፡»

وَأَوْحَيْنَا إِلَىٰ مُوسَىٰ أَنْ أَسْرِ بِعِبَادِي إِنَّكُم مُّتَّبَعُونَ
( 52 ) 
ወደ ሙሳም «ባሮቼን ይዘህ ሌሊት ኺድ፡፡ እናንተ የሚከተሉዋችሁ ናችሁና» ስንል ላክን፡፡

فَأَرْسَلَ فِرْعَوْنُ فِي الْمَدَائِنِ حَاشِرِينَ
( 53 ) 
ፈርዖንም በየከተሞቹ ሰብሳቢዎችን (እንዲህ ሲል) ላከ፡፡

إِنَّ هَٰؤُلَاءِ لَشِرْذِمَةٌ قَلِيلُونَ
( 54 ) 
«እነዚህ ጥቂቶች ጭፈሮች ናቸው፡፡

وَإِنَّهُمْ لَنَا لَغَائِظُونَ
( 55 ) 
«እነርሱም ለእኛ አስቆጪዎች ናቸው፡፡

وَإِنَّا لَجَمِيعٌ حَاذِرُونَ
( 56 ) 
«እኛም ብዙዎች ጥንቁቆች ነን፤» (አለ)፡፡

فَأَخْرَجْنَاهُم مِّن جَنَّاتٍ وَعُيُونٍ
( 57 ) 
አወጣናቸውም፡፡ ከአትክልቶችና ከምንጮች፡፡

وَكُنُوزٍ وَمَقَامٍ كَرِيمٍ
( 58 ) 
ከድልቦችም ከመልካም መቀመጫዎችም፡፡

كَذَٰلِكَ وَأَوْرَثْنَاهَا بَنِي إِسْرَائِيلَ
( 59 ) 
እንደዚሁ ለእስራኤል ልጆች አወረስናትም፡፡

فَأَتْبَعُوهُم مُّشْرِقِينَ
( 60 ) 
ፀሐይዋ ስትወጣም ተከተሉዋቸው፡፡

فَلَمَّا تَرَاءَى الْجَمْعَانِ قَالَ أَصْحَابُ مُوسَىٰ إِنَّا لَمُدْرَكُونَ
( 61 ) 
ሁለቱ ጭፍሮችም በተያዩ ጊዜ የሙሳ ጓዶች «እኛ(የፈርዖን ሰዎች) የሚደርሱብን ነን» አሉ፡፡

قَالَ كَلَّا ۖ إِنَّ مَعِيَ رَبِّي سَيَهْدِينِ
( 62 ) 
(ሙሳ) «ተዉዉ! ጌታዬ ከእኔ ጋር ነው፡፡ በእርግጥ ይመራኛል» አለ፡፡

فَأَوْحَيْنَا إِلَىٰ مُوسَىٰ أَنِ اضْرِب بِّعَصَاكَ الْبَحْرَ ۖ فَانفَلَقَ فَكَانَ كُلُّ فِرْقٍ كَالطَّوْدِ الْعَظِيمِ
( 63 ) 
ወደ ሙሳም «ባሕሩን በበትርህ ምታው» ስንል ላክንበት፡፡ (መታውና) ተከፈለም፡፡ ክፍሉም ሁሉ እንደ ታላቅ ጋራ ኾነ፡፡

وَأَزْلَفْنَا ثَمَّ الْآخَرِينَ
( 64 ) 
እዚያም ዘንድ ሌሎችን አቀረብን፡፡

وَأَنجَيْنَا مُوسَىٰ وَمَن مَّعَهُ أَجْمَعِينَ
( 65 ) 
ሙሳንም ከእርሱ ገር ያሉትንም ሰዎች ሁሉንም አዳን፡፡

ثُمَّ أَغْرَقْنَا الْآخَرِينَ
( 66 ) 
ከዚያም ሌሎቹን አሰጠምን፡፡

إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَآيَةً ۖ وَمَا كَانَ أَكْثَرُهُم مُّؤْمِنِينَ
( 67 ) 
በዚህ ውስጥ ታላቅ ታምር አለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም አማኞች አልነበሩም፡፡

وَإِنَّ رَبَّكَ لَهُوَ الْعَزِيزُ الرَّحِيمُ
( 68 ) 
ጌታህም እርሱ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡

وَاتْلُ عَلَيْهِمْ نَبَأَ إِبْرَاهِيمَ
( 69 ) 
በእነሱም (በሕዝቦችህ) ላይ የኢብራሂምን ወሬ አንብብላቸው፡፡

إِذْ قَالَ لِأَبِيهِ وَقَوْمِهِ مَا تَعْبُدُونَ
( 70 ) 
ለአባቱና ለሕዝቦቹ «ምንን ትግገዛላችሁ» ባለ ጊዜ፡፡

قَالُوا نَعْبُدُ أَصْنَامًا فَنَظَلُّ لَهَا عَاكِفِينَ
( 71 ) 
«ጣዖታትን እንገዛለን፤ እርሷንም በመገዛት ላይ እንቆያለን» አሉ፡፡

قَالَ هَلْ يَسْمَعُونَكُمْ إِذْ تَدْعُونَ
( 72 ) 
(እርሱም) አለ «በጠራችኋቸው ጊዜ ይሰሟችኋልን

أَوْ يَنفَعُونَكُمْ أَوْ يَضُرُّونَ
( 73 ) 
«ወይስ ይጠቅሟችኋልን ወይስ ይጎዷችኋልን»

قَالُوا بَلْ وَجَدْنَا آبَاءَنَا كَذَٰلِكَ يَفْعَلُونَ
( 74 ) 
«የለም! አባቶቻችን እንደዚሁ ሲሠሩ አገኘን» አሉት፡፡

قَالَ أَفَرَأَيْتُم مَّا كُنتُمْ تَعْبُدُونَ
( 75 ) 
«ትግገዙት የነበራችሁትን አስተዋላችሁን

أَنتُمْ وَآبَاؤُكُمُ الْأَقْدَمُونَ
( 76 ) 
«እናንተም የቀድሞዎቹ አባቶቻችሁም (የተግገዛችሁትን)፡፡»

فَإِنَّهُمْ عَدُوٌّ لِّي إِلَّا رَبَّ الْعَالَمِينَ
( 77 ) 
«እነሱም (ጣዖቶቹ) ለእኔ ጠላቶች ናቸው፡፡ ግን የዓለማት ጌታ ሲቀር (እርሱ ወዳጄ ነው)፡፡

الَّذِي خَلَقَنِي فَهُوَ يَهْدِينِ
( 78 ) 
«(እርሱ) ያ የፈጠረኝ ነው፡፡ እርሱም ይመራኛል፡፡

وَالَّذِي هُوَ يُطْعِمُنِي وَيَسْقِينِ
( 79 ) 
«ያም እርሱ የሚያበላኝና የሚያጠጣኝ ነው፡፡

وَإِذَا مَرِضْتُ فَهُوَ يَشْفِينِ
( 80 ) 
«በታመምኩም ጊዜ እርሱ ያሽረኛል፡፡

وَالَّذِي يُمِيتُنِي ثُمَّ يُحْيِينِ
( 81 ) 
«ያም የሚገድለኝ ከዚያም ሕያው የሚያደርገኝ ነው፡፡

وَالَّذِي أَطْمَعُ أَن يَغْفِرَ لِي خَطِيئَتِي يَوْمَ الدِّينِ
( 82 ) 
ያም በፍርዱ ቀን ኀጢአቴን ለእኔ ሊምር የምከጅለው ነው፡፡

رَبِّ هَبْ لِي حُكْمًا وَأَلْحِقْنِي بِالصَّالِحِينَ
( 83 ) 
ጌታዬ ሆይ! ዕውቀትን ስጠኝ! በደጋጎቹም ሰዎች አስጠጋኝ፡፡

وَاجْعَل لِّي لِسَانَ صِدْقٍ فِي الْآخِرِينَ
( 84 ) 
በኋለኞቹም ሕዝቦች ውስጥ ለእኔ መልካም ዝናን አድርግልኝ፡፡

وَاجْعَلْنِي مِن وَرَثَةِ جَنَّةِ النَّعِيمِ
( 85 ) 
የጸጋይቱን ገነት ከሚወርሱትም አድርገኝ፡፡

وَاغْفِرْ لِأَبِي إِنَّهُ كَانَ مِنَ الضَّالِّينَ
( 86 ) 
ለአባቴም ማር፡፡ እርሱ ከተሳሳቱት ነበረና፡፡

وَلَا تُخْزِنِي يَوْمَ يُبْعَثُونَ
( 87 ) 
በሚቀሰቀሱበት ቀንም አታዋርደኝ፡፡

يَوْمَ لَا يَنفَعُ مَالٌ وَلَا بَنُونَ
( 88 ) 
ገንዘብም ልጆችም በማይጠቅሙበት ቀን፡፡

إِلَّا مَنْ أَتَى اللَّهَ بِقَلْبٍ سَلِيمٍ
( 89 ) 
ወደ አላህ በንጹህ ልብ የመጣ ሰው ቢኾን እንጅ፡፡»

وَأُزْلِفَتِ الْجَنَّةُ لِلْمُتَّقِينَ
( 90 ) 
ገነትም ለፈሪዎች በምትቀረብበት (ቀን)፡፡

وَبُرِّزَتِ الْجَحِيمُ لِلْغَاوِينَ
( 91 ) 
ገሀነምም ለጠመሞች በምትገለጽበት (ቀን)፡፡

وَقِيلَ لَهُمْ أَيْنَ مَا كُنتُمْ تَعْبُدُونَ
( 92 ) 
ለእነሱም በሚባል ቀን «ትግገዟቸው የነበራችሁት የት ናቸው»

مِن دُونِ اللَّهِ هَلْ يَنصُرُونَكُمْ أَوْ يَنتَصِرُونَ
( 93 ) 
«ከአላህ ሌላ ሲኾኑ ይረዱዋችኋልን ወይስ (ለራሳቸው) ይርረዳሉን»

فَكُبْكِبُوا فِيهَا هُمْ وَالْغَاوُونَ
( 94 ) 
በውስጧም እነሱና ጠማሞቹ በፊቶቻቸው ተጥለው ይንከባለላሉ፡፡

وَجُنُودُ إِبْلِيسَ أَجْمَعُونَ
( 95 ) 
የሰይጣንም ሰራዊቶች መላውም (ይጣላሉ)፡፡

قَالُوا وَهُمْ فِيهَا يَخْتَصِمُونَ
( 96 ) 
እነርሱም በእርሷ ውስጥ የሚከራከሩ ኾነው ይላሉ፡-

تَاللَّهِ إِن كُنَّا لَفِي ضَلَالٍ مُّبِينٍ
( 97 ) 
በአላህ እንምላለን፤ እኛ በግልጽ መሳሳት ውስጥ ነበርን፡፡

إِذْ نُسَوِّيكُم بِرَبِّ الْعَالَمِينَ
( 98 ) 
(ጣዖቶቹን) በዓለማት ጌታ ባስተካከልናችሁ ጊዜ፡፡

وَمَا أَضَلَّنَا إِلَّا الْمُجْرِمُونَ
( 99 ) 
አመጸኞቹም እንጅ ሌላ አላሳሳተንም፡፡

فَمَا لَنَا مِن شَافِعِينَ
( 100 ) 
ከአማላጆችም ለእኛ ምንም የለንም፡፡

وَلَا صَدِيقٍ حَمِيمٍ
( 101 ) 
አዛኝ ወዳጂም (የለንም)፡፡

فَلَوْ أَنَّ لَنَا كَرَّةً فَنَكُونَ مِنَ الْمُؤْمِنِينَ
( 102 ) 
ለእኛም አንዲት ጊዜ መመለስ በኖረችንና ከአማኞቹ በኾን እንመኛለን (ይላሉ)፡፡

إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَآيَةً ۖ وَمَا كَانَ أَكْثَرُهُم مُّؤْمِنِينَ
( 103 ) 
በዚህ ውስጥ አስደናቂ ግሳጼ አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም አማኞች አልነበሩም፡፡

وَإِنَّ رَبَّكَ لَهُوَ الْعَزِيزُ الرَّحِيمُ
( 104 ) 
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡

كَذَّبَتْ قَوْمُ نُوحٍ الْمُرْسَلِينَ
( 105 ) 
የኑሕ ሕዝቦች መልክተኞችን አስተባበሉ፡፡

إِذْ قَالَ لَهُمْ أَخُوهُمْ نُوحٌ أَلَا تَتَّقُونَ
( 106 ) 
ወንድማቸው ኑሕ ለእነሱ ባላቸው ጊዜ «አትጠነቀቁምን

إِنِّي لَكُمْ رَسُولٌ أَمِينٌ
( 107 ) 
«እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡

فَاتَّقُوا اللَّهَ وَأَطِيعُونِ
( 108 ) 
«አላህንም ፍሩ ታዘዙኝም፡፡

وَمَا أَسْأَلُكُمْ عَلَيْهِ مِنْ أَجْرٍ ۖ إِنْ أَجْرِيَ إِلَّا عَلَىٰ رَبِّ الْعَالَمِينَ
( 109 ) 
«በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ አልጠይቃችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡

فَاتَّقُوا اللَّهَ وَأَطِيعُونِ
( 110 ) 
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡»

قَالُوا أَنُؤْمِنُ لَكَ وَاتَّبَعَكَ الْأَرْذَلُونَ
( 111 ) 
(እነርሱም) «ወራዶቹ የተከተሉህ ኾነህ ለአንተ እናምናለን» አሉት፡፡

قَالَ وَمَا عِلْمِي بِمَا كَانُوا يَعْمَلُونَ
( 112 ) 
(እርሱም) አላቸው «ይሠሩት በነበሩት ነገር ምን ዕውቀት አለኝ፡፡

إِنْ حِسَابُهُمْ إِلَّا عَلَىٰ رَبِّي ۖ لَوْ تَشْعُرُونَ
( 113 ) 
«ምርመራቸው በጌታዬ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡ ብታውቁ ኖሮ (ይህንን ትርረዱ ነበር)፡፡

وَمَا أَنَا بِطَارِدِ الْمُؤْمِنِينَ
( 114 ) 
«እኔም አማኞችን አባራሪ አይደለሁም፡፡

إِنْ أَنَا إِلَّا نَذِيرٌ مُّبِينٌ
( 115 ) 
«እኔ ግልጽ አስፈራሪ እንጅ ሌላ አይደለሁም፡፡»

قَالُوا لَئِن لَّمْ تَنتَهِ يَا نُوحُ لَتَكُونَنَّ مِنَ الْمَرْجُومِينَ
( 116 ) 
«ኑሕ ሆይ! (ከምትለው) ባትከለከል በእርግጥ ከሚወገሩት ትኾናለህ» አሉት፡፡

قَالَ رَبِّ إِنَّ قَوْمِي كَذَّبُونِ
( 117 ) 
(እርሱም) አለ «ጌታዬ ሆይ! ሕዝቦቼ አስተባበሉኝ፡፡

فَافْتَحْ بَيْنِي وَبَيْنَهُمْ فَتْحًا وَنَجِّنِي وَمَن مَّعِيَ مِنَ الْمُؤْمِنِينَ
( 118 ) 
«በእኔና በእነርሱም መካከል (ተገቢ) ፍርድን ፍረድ፡፡ አድነኝም፡፡ ከእኔ ጋር ያሉትንም ምእምናን፡፡»

فَأَنجَيْنَاهُ وَمَن مَّعَهُ فِي الْفُلْكِ الْمَشْحُونِ
( 119 ) 
እርሱንም ከእርሱ ጋር ያለውንም ሁሉ በተመላው መርከብ ውስጥ አዳን፡፡

ثُمَّ أَغْرَقْنَا بَعْدُ الْبَاقِينَ
( 120 ) 
ከዚያም በኋላ ቀሪዎቹን አሰጠምን፡፡

إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَآيَةً ۖ وَمَا كَانَ أَكْثَرُهُم مُّؤْمِنِينَ
( 121 ) 
በዚህ ውስጥ ታላቅ ግሳጼ አለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም አማኞች አልነበሩም፡፡

وَإِنَّ رَبَّكَ لَهُوَ الْعَزِيزُ الرَّحِيمُ
( 122 ) 
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡

كَذَّبَتْ عَادٌ الْمُرْسَلِينَ
( 123 ) 
ዓድ መልክተኞችን አስተባበለች፡፡

إِذْ قَالَ لَهُمْ أَخُوهُمْ هُودٌ أَلَا تَتَّقُونَ
( 124 ) 
ወንድማቸው ሁድ ለነርሱ ባላቸው ጊዜ «አትጠነቀቁምን

إِنِّي لَكُمْ رَسُولٌ أَمِينٌ
( 125 ) 
«እኔ ለናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡

فَاتَّقُوا اللَّهَ وَأَطِيعُونِ
( 126 ) 
«አላህንም ፍሩ ታዘዙኝም፡፡

وَمَا أَسْأَلُكُمْ عَلَيْهِ مِنْ أَجْرٍ ۖ إِنْ أَجْرِيَ إِلَّا عَلَىٰ رَبِّ الْعَالَمِينَ
( 127 ) 
«በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ አለምናችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡

أَتَبْنُونَ بِكُلِّ رِيعٍ آيَةً تَعْبَثُونَ
( 128 ) 
«የምትጫወቱ ኾናችሁ በከፍተኛ ስፍራ ሁሉ ላይ ምልክትን ትገነባላችሁን

وَتَتَّخِذُونَ مَصَانِعَ لَعَلَّكُمْ تَخْلُدُونَ
( 129 ) 
«የውሃ ማጠራቀሚያዎችንና ሕንፃዎችንም ዘላለም መኖርን የምትከጅሉ ኾናችሁ ትሠራላችሁን

وَإِذَا بَطَشْتُم بَطَشْتُمْ جَبَّارِينَ
( 130 ) 
«በቀጣችሁም ጊዜ ጨካኞች ኾናችሁ ትቀጣላችሁን

فَاتَّقُوا اللَّهَ وَأَطِيعُونِ
( 131 ) 
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡

وَاتَّقُوا الَّذِي أَمَدَّكُم بِمَا تَعْلَمُونَ
( 132 ) 
«ያንንም በምታውቁት (ጸጋ) ያጣቀማችሁን ፍሩ፡፡

أَمَدَّكُم بِأَنْعَامٍ وَبَنِينَ
( 133 ) 
«በእንስሳዎችና በልጆች ያጣቀማችሁን፡፡

وَجَنَّاتٍ وَعُيُونٍ
( 134 ) 
«በአትክልቶችና በምንጮችም፡፡

إِنِّي أَخَافُ عَلَيْكُمْ عَذَابَ يَوْمٍ عَظِيمٍ
( 135 ) 
«እኔ በእናንተ ላይ የታላቅን ቀን ቅጣት እፈራለሁና፡፡»

قَالُوا سَوَاءٌ عَلَيْنَا أَوَعَظْتَ أَمْ لَمْ تَكُن مِّنَ الْوَاعِظِينَ
( 136 ) 
(እነርሱም) አሉ «ብትገስጽም ወይም ከገሳጮቹ ባትኾንም በእኛ ላይ እኩል ነው፤ (ያለንበትን አንለቅም)፡፡

إِنْ هَٰذَا إِلَّا خُلُقُ الْأَوَّلِينَ
( 137 ) 
«ይህ የፊተኞቹ ሰዎች ፀባይ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡

وَمَا نَحْنُ بِمُعَذَّبِينَ
( 138 ) 
«እኛም የምንቅቀጣ አይደለንም» (አሉ)፡፡

فَكَذَّبُوهُ فَأَهْلَكْنَاهُمْ ۗ إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَآيَةً ۖ وَمَا كَانَ أَكْثَرُهُم مُّؤْمِنِينَ
( 139 ) 
አስተባበሉትም፡፡ አጠፋናቸውም፡፡ በዚህም ውስጥ እርግጠኛ ግሳጼ አለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም ምእመናን አልነበሩም፡፡

وَإِنَّ رَبَّكَ لَهُوَ الْعَزِيزُ الرَّحِيمُ
( 140 ) 
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡

كَذَّبَتْ ثَمُودُ الْمُرْسَلِينَ
( 141 ) 
ሰሙድ መልክተኞችን አስተባበለች፡፡

إِذْ قَالَ لَهُمْ أَخُوهُمْ صَالِحٌ أَلَا تَتَّقُونَ
( 142 ) 
ወንድማቸው ሷሊህ ለእነርሱ ባላቸው ጊዜ «አትጠነቀቁምን

إِنِّي لَكُمْ رَسُولٌ أَمِينٌ
( 143 ) 
«እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡

فَاتَّقُوا اللَّهَ وَأَطِيعُونِ
( 144 ) 
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡

وَمَا أَسْأَلُكُمْ عَلَيْهِ مِنْ أَجْرٍ ۖ إِنْ أَجْرِيَ إِلَّا عَلَىٰ رَبِّ الْعَالَمِينَ
( 145 ) 
«በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ አልለምናችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡

أَتُتْرَكُونَ فِي مَا هَاهُنَا آمِنِينَ
( 146 ) 
«በዚያ እዚህ ባለው (ጸጋ) ውስጥ የረካችሁ ኾናችሁ ትተዋላችሁን

فِي جَنَّاتٍ وَعُيُونٍ
( 147 ) 
«በአትክልቶችና በምንጮች ውስጥ፡፡

وَزُرُوعٍ وَنَخْلٍ طَلْعُهَا هَضِيمٌ
( 148 ) 
«በአዝመራዎችም ፍሬዋ የበሰለ በኾነች ዘንባባም፤ (ውስጥ ትተዋላችሁን)

وَتَنْحِتُونَ مِنَ الْجِبَالِ بُيُوتًا فَارِهِينَ
( 149 ) 
«ብልሆች ኾናችሁ ከጋራዎች ቤቶችንም ትጠርባላችሁ፡፡

فَاتَّقُوا اللَّهَ وَأَطِيعُونِ
( 150 ) 
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡

وَلَا تُطِيعُوا أَمْرَ الْمُسْرِفِينَ
( 151 ) 
«የወሰን አላፊዎችንም ትዕዛዝ አትከተሉ፡፡

الَّذِينَ يُفْسِدُونَ فِي الْأَرْضِ وَلَا يُصْلِحُونَ
( 152 ) 
«የእነዚያን በምድር ላይ የሚያጠፉትንና የማያበጁትን፡፡»

قَالُوا إِنَّمَا أَنتَ مِنَ الْمُسَحَّرِينَ
( 153 ) 
(እነሱም) አሉ «አንተ በብዙ ከተደገመባቸው ሰዎች ብቻ ነህ፡፡

مَا أَنتَ إِلَّا بَشَرٌ مِّثْلُنَا فَأْتِ بِآيَةٍ إِن كُنتَ مِنَ الصَّادِقِينَ
( 154 ) 
«አንተ ብጤያችን ሰው እንጅ ሌላ አይደለህም፡፡ ከእውነተኞቹም እንደኾንክ ተዓምርን አምጣ፡፡»

قَالَ هَٰذِهِ نَاقَةٌ لَّهَا شِرْبٌ وَلَكُمْ شِرْبُ يَوْمٍ مَّعْلُومٍ
( 155 ) 
(እርሱም) አለ «ይህች ግመል ናት፡፡ ለእርሷ የመጠጥ ፋንታ አላት፡፡ ለእናንተም የታወቀ ቀን ፋንታ አላችሁ፡፡

وَلَا تَمَسُّوهَا بِسُوءٍ فَيَأْخُذَكُمْ عَذَابُ يَوْمٍ عَظِيمٍ
( 156 ) 
«በክፉም አትንኳት፡፡ የታላቅ ቀን ቅጣት ይይዛችኋልና፡፡»

فَعَقَرُوهَا فَأَصْبَحُوا نَادِمِينَ
( 157 ) 
ወጓትም፡፡ ወዲያውም ተጸጻቾች ኾነው አነጉ፡፡

فَأَخَذَهُمُ الْعَذَابُ ۗ إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَآيَةً ۖ وَمَا كَانَ أَكْثَرُهُم مُّؤْمِنِينَ
( 158 ) 
ቅጣቱም ያዛቸው፡፡ በዚህም ውስጥ ግሳፄ አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም ምእመናን አልነበሩም፡፡

وَإِنَّ رَبَّكَ لَهُوَ الْعَزِيزُ الرَّحِيمُ
( 159 ) 
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡

كَذَّبَتْ قَوْمُ لُوطٍ الْمُرْسَلِينَ
( 160 ) 
የሉጥ ሕዝቦች መልክተኞችን አስተባባሉ፡፡

إِذْ قَالَ لَهُمْ أَخُوهُمْ لُوطٌ أَلَا تَتَّقُونَ
( 161 ) 
ወንድማቸው ሉጥ ለእነርሱ ባለ ጊዜ «አትጠነቀቁምን

إِنِّي لَكُمْ رَسُولٌ أَمِينٌ
( 162 ) 
«እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡

فَاتَّقُوا اللَّهَ وَأَطِيعُونِ
( 163 ) 
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡

وَمَا أَسْأَلُكُمْ عَلَيْهِ مِنْ أَجْرٍ ۖ إِنْ أَجْرِيَ إِلَّا عَلَىٰ رَبِّ الْعَالَمِينَ
( 164 ) 
«በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ አልለምናችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡

أَتَأْتُونَ الذُّكْرَانَ مِنَ الْعَالَمِينَ
( 165 ) 
«ከዓለማት ሰዎች ወንዶችን ትመጣላችሁን

وَتَذَرُونَ مَا خَلَقَ لَكُمْ رَبُّكُم مِّنْ أَزْوَاجِكُم ۚ بَلْ أَنتُمْ قَوْمٌ عَادُونَ
( 166 ) 
«ከሚስቶቻችሁም ጌታችሁ ለናንተ የፈጠረላችሁን ትተዋላችሁን በእውነቱ እናንተ ወሰን አላፊዎች ሕዝቦ ናችሁ፡፡»

قَالُوا لَئِن لَّمْ تَنتَهِ يَا لُوطُ لَتَكُونَنَّ مِنَ الْمُخْرَجِينَ
( 167 ) 
(እነርሱም) አሉ «ሉጥ ሆይ! ባትከለከል በእርግጥ (ከአገር) ከሚወጡት ትኾናለህ፡፡»

قَالَ إِنِّي لِعَمَلِكُم مِّنَ الْقَالِينَ
( 168 ) 
(እርሱም) አለ «እኔ ሥራችሁን ከሚጠሉት ሰዎች ነኝ፡፡

رَبِّ نَجِّنِي وَأَهْلِي مِمَّا يَعْمَلُونَ
( 169 ) 
«ጌታዬ ሆይ! እኔንም ቤተሰቦቼንም ከሚሠሩት ሥራ (ቅጣት) አድነን፡፡»

فَنَجَّيْنَاهُ وَأَهْلَهُ أَجْمَعِينَ
( 170 ) 
እርሱንም ቤተሰቦቹንም በጠቅላላ አዳንናቸው፡፡

إِلَّا عَجُوزًا فِي الْغَابِرِينَ
( 171 ) 
በቀሪዎቹ ውስጥ የኾነች አሮጊት ብቻ ስትቀር (እርሷ ጠፋች)፡፡

ثُمَّ دَمَّرْنَا الْآخَرِينَ
( 172 ) 
ከዚያም ሌሎቹን አጠፋን፡፡

وَأَمْطَرْنَا عَلَيْهِم مَّطَرًا ۖ فَسَاءَ مَطَرُ الْمُنذَرِينَ
( 173 ) 
በእነሱም ላይ (የድንጋይን) ዝናምን አዘነምንባቸው፡፡ የተስፈራሪዎቹም ዝናም (ምንኛ) ከፋ፡፡

إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَآيَةً ۖ وَمَا كَانَ أَكْثَرُهُم مُّؤْمِنِينَ
( 174 ) 
በዚህ ውስጥ አስደናቂ ተዓምር አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም ምእመናን አልነበሩም፡፡

وَإِنَّ رَبَّكَ لَهُوَ الْعَزِيزُ الرَّحِيمُ
( 175 ) 
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡

كَذَّبَ أَصْحَابُ الْأَيْكَةِ الْمُرْسَلِينَ
( 176 ) 
የአይከት ሰዎች መልክተኞችን አስተባበሉ፤

إِذْ قَالَ لَهُمْ شُعَيْبٌ أَلَا تَتَّقُونَ
( 177 ) 
ሹዕይብ ለእነርሱ ባላቸው ጊዜ «አትጠነቀቁምን

إِنِّي لَكُمْ رَسُولٌ أَمِينٌ
( 178 ) 
«እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡

فَاتَّقُوا اللَّهَ وَأَطِيعُونِ
( 179 ) 
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡

وَمَا أَسْأَلُكُمْ عَلَيْهِ مِنْ أَجْرٍ ۖ إِنْ أَجْرِيَ إِلَّا عَلَىٰ رَبِّ الْعَالَمِينَ
( 180 ) 
«በርሱም ላይ ምንም ዋጋ አልጠይቃችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡

أَوْفُوا الْكَيْلَ وَلَا تَكُونُوا مِنَ الْمُخْسِرِينَ
( 181 ) 
«ስፍርን ሙሉ፡፡ ከአጉዳዮቹም አትኹኑ፡፡

وَزِنُوا بِالْقِسْطَاسِ الْمُسْتَقِيمِ
( 182 ) 
«በትክክለኛ ሚዛንም መዝኑ፡፡

وَلَا تَبْخَسُوا النَّاسَ أَشْيَاءَهُمْ وَلَا تَعْثَوْا فِي الْأَرْضِ مُفْسِدِينَ
( 183 ) 
«ሰዎችንም ነገሮቻቸውን አታጉድሉባቸው፡፡ በምድርም ላይ አጥፊዎች ኾናችሁ አታበላሹ፡፡

وَاتَّقُوا الَّذِي خَلَقَكُمْ وَالْجِبِلَّةَ الْأَوَّلِينَ
( 184 ) 
«ያንንም የፈጠራችሁን የቀድሞዎቹንም ፍጡሮች (የፈጠረውን) ፍሩ፡፡»

قَالُوا إِنَّمَا أَنتَ مِنَ الْمُسَحَّرِينَ
( 185 ) 
አሉ «አንተ በብዛት ከተደገመባቸው ሰዎች ነህ፡፡

وَمَا أَنتَ إِلَّا بَشَرٌ مِّثْلُنَا وَإِن نَّظُنُّكَ لَمِنَ الْكَاذِبِينَ
( 186 ) 
«አንተም ብጤያችን ሰው እንጅ ሌላ አይደለህም፡፡ እነሆ ከውሸታሞች ነህ ብለን እንጠረጥርሃለን፡፡

فَأَسْقِطْ عَلَيْنَا كِسَفًا مِّنَ السَّمَاءِ إِن كُنتَ مِنَ الصَّادِقِينَ
( 187 ) 
«ከእውነተኞቹም እንደኾንክ በእኛ ላይ ከሰማይ ቁራጭን ጣልብን፡፡»

قَالَ رَبِّي أَعْلَمُ بِمَا تَعْمَلُونَ
( 188 ) 
«ጌታዬ የምትሠሩትን ሁሉ ዐዋቂ ነው፤» አላቸው፡፡

فَكَذَّبُوهُ فَأَخَذَهُمْ عَذَابُ يَوْمِ الظُّلَّةِ ۚ إِنَّهُ كَانَ عَذَابَ يَوْمٍ عَظِيمٍ
( 189 ) 
አስተባበሉትም፡፡ የጥላይቷ ቀን ቅጣትም ያዛቸው፡፡ እርሱ የከባድ ቀን ቅጣት ነበርና፡፡

إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَآيَةً ۖ وَمَا كَانَ أَكْثَرُهُم مُّؤْمِنِينَ
( 190 ) 
በዚህ ውስጥ አስደናቂ ተዓምር አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም ምእምናን አልነበሩም፡፡

وَإِنَّ رَبَّكَ لَهُوَ الْعَزِيزُ الرَّحِيمُ
( 191 ) 
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡

وَإِنَّهُ لَتَنزِيلُ رَبِّ الْعَالَمِينَ
( 192 ) 
እርሱም (ቁርኣን) በእርግጥ ከዓለማት ጌታ የተወረደ ነው፡፡

نَزَلَ بِهِ الرُّوحُ الْأَمِينُ
( 193 ) 
እርሱን ታማኙ መንፈስ (ጂብሪል) አወረደው፤

عَلَىٰ قَلْبِكَ لِتَكُونَ مِنَ الْمُنذِرِينَ
( 194 ) 
ከአስፈራሪዎቹ (ነቢያት) ትኾን ዘንድ በልብህ ላይ (አወረደው)፡፡

بِلِسَانٍ عَرَبِيٍّ مُّبِينٍ
( 195 ) 
ግልጽ በኾነ ዐረብኛ ቋንቋ፡፡

وَإِنَّهُ لَفِي زُبُرِ الْأَوَّلِينَ
( 196 ) 
እርሱም (ቁርኣን) በቀድሞዎቹ መጻሐፍት ውስጥ (የተወሳ ነው)፡፡

أَوَلَمْ يَكُن لَّهُمْ آيَةً أَن يَعْلَمَهُ عُلَمَاءُ بَنِي إِسْرَائِيلَ
( 197 ) 
የእስራኤል ልጆች ሊቃውንት የሚያውቁት መኾኑ ለእነርሱ (ለመካ ከሓዲዎች) ምልክት አይኾናቸውምን

وَلَوْ نَزَّلْنَاهُ عَلَىٰ بَعْضِ الْأَعْجَمِينَ
( 198 ) 
ከአዕጀሞች ባንዱ ላይ ባወረድነውም ኖሮ፤

فَقَرَأَهُ عَلَيْهِم مَّا كَانُوا بِهِ مُؤْمِنِينَ
( 199 ) 
በእነርሱ ላይ ባነበበውም በእርሱ አማኞች አይኾኑም ነበር፡፡

كَذَٰلِكَ سَلَكْنَاهُ فِي قُلُوبِ الْمُجْرِمِينَ
( 200 ) 
እንደዚሁ (ማስተባበልን) በተንኮለኞች ልቦች ውስጥ አስገባነው፡፡

لَا يُؤْمِنُونَ بِهِ حَتَّىٰ يَرَوُا الْعَذَابَ الْأَلِيمَ
( 201 ) 
አሳማሚ ቅጣትን እስከሚያዩ ድረስ በእርሱ አያምኑም፡፡

فَيَأْتِيَهُم بَغْتَةً وَهُمْ لَا يَشْعُرُونَ
( 202 ) 
እነርሱ የማያውቁ ሲኾኑ (ቅጣቱ) ድንገት እስከሚመጣባቸውም ድረስ (አያምኑም)፡፡

فَيَقُولُوا هَلْ نَحْنُ مُنظَرُونَ
( 203 ) 
(በመጣባቸው ጊዜ) «እኛ የምንቆይ ነን» እስከሚሉም (አያምኑም)፡፡

أَفَبِعَذَابِنَا يَسْتَعْجِلُونَ
( 204 ) 
በቅጣታችን ያቻኩላሉን

أَفَرَأَيْتَ إِن مَّتَّعْنَاهُمْ سِنِينَ
( 205 ) 
አየህን ብዙ ዓመታትን ብናጣቅማቸው፤

ثُمَّ جَاءَهُم مَّا كَانُوا يُوعَدُونَ
( 206 ) 
ከዚያም ያ ይስፈራሩበት የነበሩት ቢመጣባቸው፤

مَا أَغْنَىٰ عَنْهُم مَّا كَانُوا يُمَتَّعُونَ
( 207 ) 
ይጣቀሙበት የነበሩት ሁሉ ከእነሱ ምንም አያብቃቃቸውም፡፡

وَمَا أَهْلَكْنَا مِن قَرْيَةٍ إِلَّا لَهَا مُنذِرُونَ
( 208 ) 
አንዲትንም ከተማ ለእርሷ አስፈራሪዎች ያሏት (እና ያስተባበለች) ኾና እንጅ አላጠፋንም፡፡

ذِكْرَىٰ وَمَا كُنَّا ظَالِمِينَ
( 209 ) 
(ይህች) ግሳፄ ናት፡፡ በዳዮችም አልነበርንም፡፡

وَمَا تَنَزَّلَتْ بِهِ الشَّيَاطِينُ
( 210 ) 
ሰይጣናትም እርሱን (ቁርኣንን) አላወረዱትም፡፡

وَمَا يَنبَغِي لَهُمْ وَمَا يَسْتَطِيعُونَ
( 211 ) 
ለእነርሱም አይገባቸውም፤ አይችሉምም፡፡

إِنَّهُمْ عَنِ السَّمْعِ لَمَعْزُولُونَ
( 212 ) 
እነርሱ (የመላእክትን ንግግር) ከመስማት ተከለከሉ ናቸው፡፡

فَلَا تَدْعُ مَعَ اللَّهِ إِلَٰهًا آخَرَ فَتَكُونَ مِنَ الْمُعَذَّبِينَ
( 213 ) 
ከአላህም ጋር ሌላን አምላክ አትግገዛ፤ ከሚቀጡት ትኾናለህና፡፡

وَأَنذِرْ عَشِيرَتَكَ الْأَقْرَبِينَ
( 214 ) 
ቅርቦች ዘመዶችህንም አስጠንቅቅ፡፡

وَاخْفِضْ جَنَاحَكَ لِمَنِ اتَّبَعَكَ مِنَ الْمُؤْمِنِينَ
( 215 ) 
ከምእምናንም ለተከተሉህ ሰዎች ክንፍህን ዝቅ አድርግ፤ (ልዝብ ኹን)፡፡

فَإِنْ عَصَوْكَ فَقُلْ إِنِّي بَرِيءٌ مِّمَّا تَعْمَلُونَ
( 216 ) 
«እንቢ» ቢሉህም «እኔ ከምትሠሩት ንጹሕ ነኝ» በላቸው፡፡

وَتَوَكَّلْ عَلَى الْعَزِيزِ الرَّحِيمِ
( 217 ) 
አሸናፊ አዛኝ በኾነው (ጌታህ) ላይም ተጠጋ፡፡

الَّذِي يَرَاكَ حِينَ تَقُومُ
( 218 ) 
በዚያ ለሶላት በምትቆም ጊዜ በሚያይህ፡፡

وَتَقَلُّبَكَ فِي السَّاجِدِينَ
( 219 ) 
በሰጋጆች ውስጥ መዘዋወርህንም (በሚያየው ጌታህ ላይ ተጠጋ)፡፡

إِنَّهُ هُوَ السَّمِيعُ الْعَلِيمُ
( 220 ) 
እነሆ እርሱ ሰሚው ዐዋቂው ነውና፡፡

هَلْ أُنَبِّئُكُمْ عَلَىٰ مَن تَنَزَّلُ الشَّيَاطِينُ
( 221 ) 
ሰይጣናት በማን ላይ እንደሚወርዱ ልንገራችሁን

تَنَزَّلُ عَلَىٰ كُلِّ أَفَّاكٍ أَثِيمٍ
( 222 ) 
በውሸታም ኀጢአተኛ ሁሉ ላይ ይወርዳሉ፡፡

يُلْقُونَ السَّمْعَ وَأَكْثَرُهُمْ كَاذِبُونَ
( 223 ) 
የሰሙትን (ወደ ጠንቋዮች) ይጥላሉ፡፡ አብዛኞቻቸውም ውሸታሞች ናቸው፡፡

وَالشُّعَرَاءُ يَتَّبِعُهُمُ الْغَاوُونَ
( 224 ) 
ባለ ቅኔዎችንም ጠማማዎቹ ይከተሉዋቸዋል፡፡

أَلَمْ تَرَ أَنَّهُمْ فِي كُلِّ وَادٍ يَهِيمُونَ
( 225 ) 
እነርሱ በ(ንግግር) ሸለቆ ሁሉ የሚዋልሉ መኾናቸውን አታይምን

وَأَنَّهُمْ يَقُولُونَ مَا لَا يَفْعَلُونَ
( 226 ) 
እነሱም የማይሠሩትን ነገር የሚናገሩ መኾናቸውን (አታይምን)፤

إِلَّا الَّذِينَ آمَنُوا وَعَمِلُوا الصَّالِحَاتِ وَذَكَرُوا اللَّهَ كَثِيرًا وَانتَصَرُوا مِن بَعْدِ مَا ظُلِمُوا ۗ وَسَيَعْلَمُ الَّذِينَ ظَلَمُوا أَيَّ مُنقَلَبٍ يَنقَلِبُونَ
( 227 ) 
እነዚያ ያመኑና መልካም ሥራዎችን የሠሩ አላህንም በብዛት ያወሱ ከተበደሉም በኋላ (በቅኔ) የተከላከሉ ሲቀሩ፤ (እነርሱ አይወቀሱም)፡፡ እነዚያም የበደሉ (ከሞቱ በኋላ) እንዴት ያለን መመለስ እንደሚመለሱ በእርግጥ ያውቃሉ፡፡
