Surah አል አሹዐራዕ

አማርኛ Muhammad Sadiq & Sani Habib

Surah አል አሹዐራዕ - Aya count 227
Facebook Twitter Google+ Pinterest Reddit StumbleUpon Linkedin Tumblr Google Bookmarks Email
طسم ( 1 ) አል አሹዐራዕ - Aya 1
ጠ.ሰ.መ. (ጧ ሲን ሚም)፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 1
تِلْكَ آيَاتُ الْكِتَابِ الْمُبِينِ ( 2 ) አል አሹዐራዕ - Aya 2
ይህች ግልጽ ከኾነው መጽሐፍ አንቀጾች ናት፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 2
لَعَلَّكَ بَاخِعٌ نَّفْسَكَ أَلَّا يَكُونُوا مُؤْمِنِينَ ( 3 ) አል አሹዐራዕ - Aya 3
አማኞች ባለመኾናቸው፤ (በቁጭት) ነፍስህን ገዳይ መኾን ይፈራልሃል፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 3
إِن نَّشَأْ نُنَزِّلْ عَلَيْهِم مِّنَ السَّمَاءِ آيَةً فَظَلَّتْ أَعْنَاقُهُمْ لَهَا خَاضِعِينَ ( 4 ) አል አሹዐራዕ - Aya 4
ብንሻ በእነሱ ላይ ከሰማይ ተዓምረን እናወርድና አንገቶቻቸው (መሪዎቻቸው) ለእርሷ ተዋራጆች ይኾናሉ፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 4
وَمَا يَأْتِيهِم مِّن ذِكْرٍ مِّنَ الرَّحْمَٰنِ مُحْدَثٍ إِلَّا كَانُوا عَنْهُ مُعْرِضِينَ ( 5 ) አል አሹዐራዕ - Aya 5
ከአልረሕማንም ዘንድ ኣዲስ የተወረደ ቁርኣን አይመጣላቸውም፤ ከእርሱ የሚሸሹ ቢኾኑ እንጂ፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 5
فَقَدْ كَذَّبُوا فَسَيَأْتِيهِمْ أَنبَاءُ مَا كَانُوا بِهِ يَسْتَهْزِئُونَ ( 6 ) አል አሹዐራዕ - Aya 6
በእርግጥም አስተባበሉ፡፡ የዚያም በእርሱ ይሳለቁበት የነበሩት ወሬዎች (ፍጻሜ) ይመጣባቸዋል፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 6
أَوَلَمْ يَرَوْا إِلَى الْأَرْضِ كَمْ أَنبَتْنَا فِيهَا مِن كُلِّ زَوْجٍ كَرِيمٍ ( 7 ) አል አሹዐራዕ - Aya 7
ወደ ምድርም በውስጧ ከመልካም (በቃይ) ጎሳ ሁሉ ብዙን እንዳበቀልን አላዩምን፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 7
إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَآيَةً ۖ وَمَا كَانَ أَكْثَرُهُم مُّؤْمِنِينَ ( 8 ) አል አሹዐራዕ - Aya 8
በዚህ አስደናቂ ምልክት አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም አማኞች አልነበሩም፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 8
وَإِنَّ رَبَّكَ لَهُوَ الْعَزِيزُ الرَّحِيمُ ( 9 ) አል አሹዐራዕ - Aya 9
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊ አዛኝ ነው፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 9
وَإِذْ نَادَىٰ رَبُّكَ مُوسَىٰ أَنِ ائْتِ الْقَوْمَ الظَّالِمِينَ ( 10 ) አል አሹዐራዕ - Aya 10
ጌታህም ሙሳን «ወደ በደለኞቹ ሕዝቦች ኺድ» በማለት በጠራው ጊዜ (አስታውስ)፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 10
قَوْمَ فِرْعَوْنَ ۚ أَلَا يَتَّقُونَ ( 11 ) አል አሹዐራዕ - Aya 11
«ወደ ፈርዖን ሕዝቦች (ኺድ) አላህን አይፈሩምን» (አለው)፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 11
قَالَ رَبِّ إِنِّي أَخَافُ أَن يُكَذِّبُونِ ( 12 ) አል አሹዐራዕ - Aya 12
(ሙሳም) አለ «ጌታዬ ሆይ! እኔ ሊያስተባብሉኝ እፈራለሁ፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 12
وَيَضِيقُ صَدْرِي وَلَا يَنطَلِقُ لِسَانِي فَأَرْسِلْ إِلَىٰ هَارُونَ ( 13 ) አል አሹዐራዕ - Aya 13
«ልቤም ይጠብባል፡፡ ምላሴም አይፈታም፡፡ ስለዚህ ወደ ሃሩን ላክ፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 13
وَلَهُمْ عَلَيَّ ذَنبٌ فَأَخَافُ أَن يَقْتُلُونِ ( 14 ) አል አሹዐራዕ - Aya 14
«ለእነርሱም በእኔ ላይ (የደም) ወንጀል አልለ፡፡ ስለዚህ እንዳይገድሉኝ እፈራለሁ፡፡» አል አሹዐራዕ - Aya 14
قَالَ كَلَّا ۖ فَاذْهَبَا بِآيَاتِنَا ۖ إِنَّا مَعَكُم مُّسْتَمِعُونَ ( 15 ) አል አሹዐራዕ - Aya 15
(አላህ) አለ «ተው! (አይነኩህም)፡፡ በተዓምራቶቻችንም ኺዱ፡፡ እኛ ከእናንተ ጋር ሰሚዎች ነንና፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 15
فَأْتِيَا فِرْعَوْنَ فَقُولَا إِنَّا رَسُولُ رَبِّ الْعَالَمِينَ ( 16 ) አል አሹዐራዕ - Aya 16
«ወደ ፈርዖንም ኺዱ፡፡ በሉትም፡- እኛ የዓለማት ጌታ መልክተኞች ነን፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 16
أَنْ أَرْسِلْ مَعَنَا بَنِي إِسْرَائِيلَ ( 17 ) አል አሹዐራዕ - Aya 17
«የእስራኤልን ልጆች ከእኛ ጋር ልቀቅ፡፡» አል አሹዐራዕ - Aya 17
قَالَ أَلَمْ نُرَبِّكَ فِينَا وَلِيدًا وَلَبِثْتَ فِينَا مِنْ عُمُرِكَ سِنِينَ ( 18 ) አል አሹዐራዕ - Aya 18
(ፈርዖንም) አለ «ልጅ ኾነህ በእኛ ውስጥ አላሳደግንህምን በእኛ ውስጥም ከዕድሜህ ብዙ ዓመታትን አልተቀመጥክምን አል አሹዐራዕ - Aya 18
وَفَعَلْتَ فَعْلَتَكَ الَّتِي فَعَلْتَ وَأَنتَ مِنَ الْكَافِرِينَ ( 19 ) አል አሹዐራዕ - Aya 19
«ያችንም የሠራሃትን ሥራህን አልሠራህምን አንተም ከውለታ ቢሶቹ ነህ» (አለ)፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 19
قَالَ فَعَلْتُهَا إِذًا وَأَنَا مِنَ الضَّالِّينَ ( 20 ) አል አሹዐራዕ - Aya 20
(ሙሳም) አለ «ያን ጊዜ እኔም ከተሳሳቱት ኾኜ ሠራኋት፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 20
فَفَرَرْتُ مِنكُمْ لَمَّا خِفْتُكُمْ فَوَهَبَ لِي رَبِّي حُكْمًا وَجَعَلَنِي مِنَ الْمُرْسَلِينَ ( 21 ) አል አሹዐራዕ - Aya 21
«በፈራኋችሁም ጊዜ ከእንናተ ሸሸሁ፡፡ ጌታየም ለእኔ ጥበብን ሰጠኝ፡፡ ከመልክተኞቹም አደረገኝ፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 21
وَتِلْكَ نِعْمَةٌ تَمُنُّهَا عَلَيَّ أَنْ عَبَّدتَّ بَنِي إِسْرَائِيلَ ( 22 ) አል አሹዐራዕ - Aya 22
«ይህችም የእስራኤልን ልጆች ባሪያ በማድረግህ በእኔ ላይ የምትመጻደቅባት ጸጋ ነት፡፡» አል አሹዐራዕ - Aya 22
قَالَ فِرْعَوْنُ وَمَا رَبُّ الْعَالَمِينَ ( 23 ) አል አሹዐራዕ - Aya 23
ፈርዖን አለ «(ላከኝ የምትለው) የዓለማትም ጌታ ምንድነው» አል አሹዐራዕ - Aya 23
قَالَ رَبُّ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ وَمَا بَيْنَهُمَا ۖ إِن كُنتُم مُّوقِنِينَ ( 24 ) አል አሹዐራዕ - Aya 24
(ሙሳ) «የሰማያትና የምድር በመካከላቸውም ያለው ሁሉ ጌታ ነው፡፡ የምታረጋግጡ ብትኾኑ (ነገሩ ይህ ነው)፤» አለው፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 24
قَالَ لِمَنْ حَوْلَهُ أَلَا تَسْتَمِعُونَ ( 25 ) አል አሹዐራዕ - Aya 25
(ፈርዖንም) በዙሪያው ላሉት ሰዎች «አትሰሙምን» አለ፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 25
قَالَ رَبُّكُمْ وَرَبُّ آبَائِكُمُ الْأَوَّلِينَ ( 26 ) አል አሹዐራዕ - Aya 26
(ሙሳ) «ጌታችሁና የመጀመሪያዎቹ አባቶቻችሁም ጌታ ነው» አለው፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 26
قَالَ إِنَّ رَسُولَكُمُ الَّذِي أُرْسِلَ إِلَيْكُمْ لَمَجْنُونٌ ( 27 ) አል አሹዐራዕ - Aya 27
(ፈርዖን) «ያ ወደእናንተ የተላከው መልክተኛችሁ በእርግጥ ዕብድ ነው» አለ፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 27
قَالَ رَبُّ الْمَشْرِقِ وَالْمَغْرِبِ وَمَا بَيْنَهُمَا ۖ إِن كُنتُمْ تَعْقِلُونَ ( 28 ) አል አሹዐራዕ - Aya 28
(ሙሳ) «የምሥራቅና የምዕራብ በመካከላቸውም ያለው ነገር ሁሉ ጌታ ነው፡፡ ታውቁ እንደኾናችሁ (እመኑበት)» አለው፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 28
قَالَ لَئِنِ اتَّخَذْتَ إِلَٰهًا غَيْرِي لَأَجْعَلَنَّكَ مِنَ الْمَسْجُونِينَ ( 29 ) አል አሹዐራዕ - Aya 29
(ፈርዖን) «ከእኔ ሌላ አምላክን ብትይዝ በውነቱ ከእስረኞቹ አደርግሃለሁ» አለ፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 29
قَالَ أَوَلَوْ جِئْتُكَ بِشَيْءٍ مُّبِينٍ ( 30 ) አል አሹዐራዕ - Aya 30
(ሙሳ) «በግልጽ አስረጅ ብመጣህም እንኳ» አለው፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 30
قَالَ فَأْتِ بِهِ إِن كُنتَ مِنَ الصَّادِقِينَ ( 31 ) አል አሹዐራዕ - Aya 31
«እንግዲያውስ ከእውነተኞች እንደኾንክ (አስረጁን) አምጣው» አለ፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 31
فَأَلْقَىٰ عَصَاهُ فَإِذَا هِيَ ثُعْبَانٌ مُّبِينٌ ( 32 ) አል አሹዐራዕ - Aya 32
በትሩንም ጣለ፡፡ እርሷም ወዲያውኑ ግልጽ እባብ ኾነች፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 32
وَنَزَعَ يَدَهُ فَإِذَا هِيَ بَيْضَاءُ لِلنَّاظِرِينَ ( 33 ) አል አሹዐራዕ - Aya 33
እጁንም አወጣ፡፡ ወዲያውም እርሷ ለተመልካቾች (የምታበራ) ነጭ ኾነች፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 33
قَالَ لِلْمَلَإِ حَوْلَهُ إِنَّ هَٰذَا لَسَاحِرٌ عَلِيمٌ ( 34 ) አል አሹዐራዕ - Aya 34
(ፈርዖን) በዙሪያው ላሉት መማክርት «ይህ በእርግጥ ዐዋቂ ድግምተኛ ነው» አለ፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 34
يُرِيدُ أَن يُخْرِجَكُم مِّنْ أَرْضِكُم بِسِحْرِهِ فَمَاذَا تَأْمُرُونَ ( 35 ) አል አሹዐራዕ - Aya 35
«ከምድራችሁ በድግምቱ ሊያወጣችሁ ይፈልጋልና ምንን ታዛላችሁ» (አላቸው)፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 35
قَالُوا أَرْجِهْ وَأَخَاهُ وَابْعَثْ فِي الْمَدَائِنِ حَاشِرِينَ ( 36 ) አል አሹዐራዕ - Aya 36
አሉት «እርሱን ወንድሙንም አቆይና በየከተሞቹ ሰብሳቢዎችን ላክ፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 36
يَأْتُوكَ بِكُلِّ سَحَّارٍ عَلِيمٍ ( 37 ) አል አሹዐራዕ - Aya 37
«በጣም ዐዋቂ ድግምተኞችን ሁሉ ያመጡልሃልና፡፡» አል አሹዐራዕ - Aya 37
فَجُمِعَ السَّحَرَةُ لِمِيقَاتِ يَوْمٍ مَّعْلُومٍ ( 38 ) አል አሹዐራዕ - Aya 38
ድግምተኞቹም በታወቀ ቀን ቀጠሮ ተሰበሰቡ፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 38
وَقِيلَ لِلنَّاسِ هَلْ أَنتُم مُّجْتَمِعُونَ ( 39 ) አል አሹዐራዕ - Aya 39
ለሰዎቹም «እናንተ ተሰብስባችኋልን» ተባለ፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 39
لَعَلَّنَا نَتَّبِعُ السَّحَرَةَ إِن كَانُوا هُمُ الْغَالِبِينَ ( 40 ) አል አሹዐራዕ - Aya 40
«ድግምተኞቹን እነሱ አሸናፊዎች ቢኾኑ እንከተል ዘንድ» (ተባለ)፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 40
فَلَمَّا جَاءَ السَّحَرَةُ قَالُوا لِفِرْعَوْنَ أَئِنَّ لَنَا لَأَجْرًا إِن كُنَّا نَحْنُ الْغَالِبِينَ ( 41 ) አል አሹዐራዕ - Aya 41
«ድግምተኞቹም በመጡ ጊዜ ለፈርዖን እኛ አሸናፊዎች ብንሆን ለእኛ በእርግጥ ዋጋ አለን» አሉት፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 41
قَالَ نَعَمْ وَإِنَّكُمْ إِذًا لَّمِنَ الْمُقَرَّبِينَ ( 42 ) አል አሹዐራዕ - Aya 42
«አዎን፤ እናንተም ያን ጊዜ ከባለሟሎቹ ትኾናላችሁ» አላቸው፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 42
قَالَ لَهُم مُّوسَىٰ أَلْقُوا مَا أَنتُم مُّلْقُونَ ( 43 ) አል አሹዐራዕ - Aya 43
ሙሳ «ለእነርሱ እናንተ የምትጥሉትን ጣሉ» አላቸው፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 43
فَأَلْقَوْا حِبَالَهُمْ وَعِصِيَّهُمْ وَقَالُوا بِعِزَّةِ فِرْعَوْنَ إِنَّا لَنَحْنُ الْغَالِبُونَ ( 44 ) አል አሹዐራዕ - Aya 44
ገመዶቻቸውንና በትሮቻቸውንም ጣሉ፡፡ «በፈርዖንም ክብር ይኹንብን፡፡ እኛ በእርግጥ አሸናፊዎቹ እኛ ነን» አሉ፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 44
فَأَلْقَىٰ مُوسَىٰ عَصَاهُ فَإِذَا هِيَ تَلْقَفُ مَا يَأْفِكُونَ ( 45 ) አል አሹዐራዕ - Aya 45
ሙሳም በትሩን ጣለ፡፡ ወዲያውም እርሷ የሚያስመስሉትን ሁሉ ትውጣለች፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 45
فَأُلْقِيَ السَّحَرَةُ سَاجِدِينَ ( 46 ) አል አሹዐራዕ - Aya 46
ድግምተኞቹም ሰጋጆች ኾነው ወደቁ፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 46
قَالُوا آمَنَّا بِرَبِّ الْعَالَمِينَ ( 47 ) አል አሹዐራዕ - Aya 47
(እነሱም) አሉ «በዓለማት ጌታ አመንን፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 47
رَبِّ مُوسَىٰ وَهَارُونَ ( 48 ) አል አሹዐራዕ - Aya 48
«በሙሳና በሃሩን ጌታ፡፡» አል አሹዐራዕ - Aya 48
قَالَ آمَنتُمْ لَهُ قَبْلَ أَنْ آذَنَ لَكُمْ ۖ إِنَّهُ لَكَبِيرُكُمُ الَّذِي عَلَّمَكُمُ السِّحْرَ فَلَسَوْفَ تَعْلَمُونَ ۚ لَأُقَطِّعَنَّ أَيْدِيَكُمْ وَأَرْجُلَكُم مِّنْ خِلَافٍ وَلَأُصَلِّبَنَّكُمْ أَجْمَعِينَ ( 49 ) አል አሹዐራዕ - Aya 49
(ፈርዖንም) «ለእናንተ ሳልፈቅድላችሁ በፊት ለእርሱ አመናችሁን እርሱ ያ ድግምትን ያስተማራችሁ ታላቃችሁ ነው፡፡ ወደፊትም (የሚያገኛችሁን) በእርግጥ ታውቃላችሁ፡፡ እጆቻችሁንና እግሮቻችሁን (ቀኝና ግራን) በማናጋት እቆረርጣለሁ፡፡ ሁላችሁንም እሰቅላችኋለሁም» አለ፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 49
قَالُوا لَا ضَيْرَ ۖ إِنَّا إِلَىٰ رَبِّنَا مُنقَلِبُونَ ( 50 ) አል አሹዐራዕ - Aya 50
(እነርሱም) አሉ «ጉዳት የለብንም፡፡ እኛ ወደ ጌታችን ተመላሾች ነን፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 50
إِنَّا نَطْمَعُ أَن يَغْفِرَ لَنَا رَبُّنَا خَطَايَانَا أَن كُنَّا أَوَّلَ الْمُؤْمِنِينَ ( 51 ) አል አሹዐራዕ - Aya 51
«እኛ የምእምናን መጀመሪያ በመኾናችን ጌታችን ኀጢአቶቻችንን ለእኛ ሊምር እንከጅላለን፡፡» አል አሹዐራዕ - Aya 51
وَأَوْحَيْنَا إِلَىٰ مُوسَىٰ أَنْ أَسْرِ بِعِبَادِي إِنَّكُم مُّتَّبَعُونَ ( 52 ) አል አሹዐራዕ - Aya 52
ወደ ሙሳም «ባሮቼን ይዘህ ሌሊት ኺድ፡፡ እናንተ የሚከተሉዋችሁ ናችሁና» ስንል ላክን፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 52
فَأَرْسَلَ فِرْعَوْنُ فِي الْمَدَائِنِ حَاشِرِينَ ( 53 ) አል አሹዐራዕ - Aya 53
ፈርዖንም በየከተሞቹ ሰብሳቢዎችን (እንዲህ ሲል) ላከ፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 53
إِنَّ هَٰؤُلَاءِ لَشِرْذِمَةٌ قَلِيلُونَ ( 54 ) አል አሹዐራዕ - Aya 54
«እነዚህ ጥቂቶች ጭፈሮች ናቸው፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 54
وَإِنَّهُمْ لَنَا لَغَائِظُونَ ( 55 ) አል አሹዐራዕ - Aya 55
«እነርሱም ለእኛ አስቆጪዎች ናቸው፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 55
وَإِنَّا لَجَمِيعٌ حَاذِرُونَ ( 56 ) አል አሹዐራዕ - Aya 56
«እኛም ብዙዎች ጥንቁቆች ነን፤» (አለ)፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 56
فَأَخْرَجْنَاهُم مِّن جَنَّاتٍ وَعُيُونٍ ( 57 ) አል አሹዐራዕ - Aya 57
አወጣናቸውም፡፡ ከአትክልቶችና ከምንጮች፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 57
وَكُنُوزٍ وَمَقَامٍ كَرِيمٍ ( 58 ) አል አሹዐራዕ - Aya 58
ከድልቦችም ከመልካም መቀመጫዎችም፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 58
كَذَٰلِكَ وَأَوْرَثْنَاهَا بَنِي إِسْرَائِيلَ ( 59 ) አል አሹዐራዕ - Aya 59
እንደዚሁ ለእስራኤል ልጆች አወረስናትም፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 59
فَأَتْبَعُوهُم مُّشْرِقِينَ ( 60 ) አል አሹዐራዕ - Aya 60
ፀሐይዋ ስትወጣም ተከተሉዋቸው፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 60
فَلَمَّا تَرَاءَى الْجَمْعَانِ قَالَ أَصْحَابُ مُوسَىٰ إِنَّا لَمُدْرَكُونَ ( 61 ) አል አሹዐራዕ - Aya 61
ሁለቱ ጭፍሮችም በተያዩ ጊዜ የሙሳ ጓዶች «እኛ(የፈርዖን ሰዎች) የሚደርሱብን ነን» አሉ፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 61
قَالَ كَلَّا ۖ إِنَّ مَعِيَ رَبِّي سَيَهْدِينِ ( 62 ) አል አሹዐራዕ - Aya 62
(ሙሳ) «ተዉዉ! ጌታዬ ከእኔ ጋር ነው፡፡ በእርግጥ ይመራኛል» አለ፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 62
فَأَوْحَيْنَا إِلَىٰ مُوسَىٰ أَنِ اضْرِب بِّعَصَاكَ الْبَحْرَ ۖ فَانفَلَقَ فَكَانَ كُلُّ فِرْقٍ كَالطَّوْدِ الْعَظِيمِ ( 63 ) አል አሹዐራዕ - Aya 63
ወደ ሙሳም «ባሕሩን በበትርህ ምታው» ስንል ላክንበት፡፡ (መታውና) ተከፈለም፡፡ ክፍሉም ሁሉ እንደ ታላቅ ጋራ ኾነ፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 63
وَأَزْلَفْنَا ثَمَّ الْآخَرِينَ ( 64 ) አል አሹዐራዕ - Aya 64
እዚያም ዘንድ ሌሎችን አቀረብን፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 64
وَأَنجَيْنَا مُوسَىٰ وَمَن مَّعَهُ أَجْمَعِينَ ( 65 ) አል አሹዐራዕ - Aya 65
ሙሳንም ከእርሱ ገር ያሉትንም ሰዎች ሁሉንም አዳን፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 65
ثُمَّ أَغْرَقْنَا الْآخَرِينَ ( 66 ) አል አሹዐራዕ - Aya 66
ከዚያም ሌሎቹን አሰጠምን፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 66
إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَآيَةً ۖ وَمَا كَانَ أَكْثَرُهُم مُّؤْمِنِينَ ( 67 ) አል አሹዐራዕ - Aya 67
በዚህ ውስጥ ታላቅ ታምር አለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም አማኞች አልነበሩም፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 67
وَإِنَّ رَبَّكَ لَهُوَ الْعَزِيزُ الرَّحِيمُ ( 68 ) አል አሹዐራዕ - Aya 68
ጌታህም እርሱ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 68
وَاتْلُ عَلَيْهِمْ نَبَأَ إِبْرَاهِيمَ ( 69 ) አል አሹዐራዕ - Aya 69
በእነሱም (በሕዝቦችህ) ላይ የኢብራሂምን ወሬ አንብብላቸው፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 69
إِذْ قَالَ لِأَبِيهِ وَقَوْمِهِ مَا تَعْبُدُونَ ( 70 ) አል አሹዐራዕ - Aya 70
ለአባቱና ለሕዝቦቹ «ምንን ትግገዛላችሁ» ባለ ጊዜ፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 70
قَالُوا نَعْبُدُ أَصْنَامًا فَنَظَلُّ لَهَا عَاكِفِينَ ( 71 ) አል አሹዐራዕ - Aya 71
«ጣዖታትን እንገዛለን፤ እርሷንም በመገዛት ላይ እንቆያለን» አሉ፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 71
قَالَ هَلْ يَسْمَعُونَكُمْ إِذْ تَدْعُونَ ( 72 ) አል አሹዐራዕ - Aya 72
(እርሱም) አለ «በጠራችኋቸው ጊዜ ይሰሟችኋልን አል አሹዐራዕ - Aya 72
أَوْ يَنفَعُونَكُمْ أَوْ يَضُرُّونَ ( 73 ) አል አሹዐራዕ - Aya 73
«ወይስ ይጠቅሟችኋልን ወይስ ይጎዷችኋልን» አል አሹዐራዕ - Aya 73
قَالُوا بَلْ وَجَدْنَا آبَاءَنَا كَذَٰلِكَ يَفْعَلُونَ ( 74 ) አል አሹዐራዕ - Aya 74
«የለም! አባቶቻችን እንደዚሁ ሲሠሩ አገኘን» አሉት፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 74
قَالَ أَفَرَأَيْتُم مَّا كُنتُمْ تَعْبُدُونَ ( 75 ) አል አሹዐራዕ - Aya 75
«ትግገዙት የነበራችሁትን አስተዋላችሁን አል አሹዐራዕ - Aya 75
أَنتُمْ وَآبَاؤُكُمُ الْأَقْدَمُونَ ( 76 ) አል አሹዐራዕ - Aya 76
«እናንተም የቀድሞዎቹ አባቶቻችሁም (የተግገዛችሁትን)፡፡» አል አሹዐራዕ - Aya 76
فَإِنَّهُمْ عَدُوٌّ لِّي إِلَّا رَبَّ الْعَالَمِينَ ( 77 ) አል አሹዐራዕ - Aya 77
«እነሱም (ጣዖቶቹ) ለእኔ ጠላቶች ናቸው፡፡ ግን የዓለማት ጌታ ሲቀር (እርሱ ወዳጄ ነው)፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 77
الَّذِي خَلَقَنِي فَهُوَ يَهْدِينِ ( 78 ) አል አሹዐራዕ - Aya 78
«(እርሱ) ያ የፈጠረኝ ነው፡፡ እርሱም ይመራኛል፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 78
وَالَّذِي هُوَ يُطْعِمُنِي وَيَسْقِينِ ( 79 ) አል አሹዐራዕ - Aya 79
«ያም እርሱ የሚያበላኝና የሚያጠጣኝ ነው፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 79
وَإِذَا مَرِضْتُ فَهُوَ يَشْفِينِ ( 80 ) አል አሹዐራዕ - Aya 80
«በታመምኩም ጊዜ እርሱ ያሽረኛል፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 80
وَالَّذِي يُمِيتُنِي ثُمَّ يُحْيِينِ ( 81 ) አል አሹዐራዕ - Aya 81
«ያም የሚገድለኝ ከዚያም ሕያው የሚያደርገኝ ነው፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 81
وَالَّذِي أَطْمَعُ أَن يَغْفِرَ لِي خَطِيئَتِي يَوْمَ الدِّينِ ( 82 ) አል አሹዐራዕ - Aya 82
ያም በፍርዱ ቀን ኀጢአቴን ለእኔ ሊምር የምከጅለው ነው፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 82
رَبِّ هَبْ لِي حُكْمًا وَأَلْحِقْنِي بِالصَّالِحِينَ ( 83 ) አል አሹዐራዕ - Aya 83
ጌታዬ ሆይ! ዕውቀትን ስጠኝ! በደጋጎቹም ሰዎች አስጠጋኝ፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 83
وَاجْعَل لِّي لِسَانَ صِدْقٍ فِي الْآخِرِينَ ( 84 ) አል አሹዐራዕ - Aya 84
በኋለኞቹም ሕዝቦች ውስጥ ለእኔ መልካም ዝናን አድርግልኝ፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 84
وَاجْعَلْنِي مِن وَرَثَةِ جَنَّةِ النَّعِيمِ ( 85 ) አል አሹዐራዕ - Aya 85
የጸጋይቱን ገነት ከሚወርሱትም አድርገኝ፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 85
وَاغْفِرْ لِأَبِي إِنَّهُ كَانَ مِنَ الضَّالِّينَ ( 86 ) አል አሹዐራዕ - Aya 86
ለአባቴም ማር፡፡ እርሱ ከተሳሳቱት ነበረና፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 86
وَلَا تُخْزِنِي يَوْمَ يُبْعَثُونَ ( 87 ) አል አሹዐራዕ - Aya 87
በሚቀሰቀሱበት ቀንም አታዋርደኝ፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 87
يَوْمَ لَا يَنفَعُ مَالٌ وَلَا بَنُونَ ( 88 ) አል አሹዐራዕ - Aya 88
ገንዘብም ልጆችም በማይጠቅሙበት ቀን፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 88
إِلَّا مَنْ أَتَى اللَّهَ بِقَلْبٍ سَلِيمٍ ( 89 ) አል አሹዐራዕ - Aya 89
ወደ አላህ በንጹህ ልብ የመጣ ሰው ቢኾን እንጅ፡፡» አል አሹዐራዕ - Aya 89
وَأُزْلِفَتِ الْجَنَّةُ لِلْمُتَّقِينَ ( 90 ) አል አሹዐራዕ - Aya 90
ገነትም ለፈሪዎች በምትቀረብበት (ቀን)፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 90
وَبُرِّزَتِ الْجَحِيمُ لِلْغَاوِينَ ( 91 ) አል አሹዐራዕ - Aya 91
ገሀነምም ለጠመሞች በምትገለጽበት (ቀን)፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 91
وَقِيلَ لَهُمْ أَيْنَ مَا كُنتُمْ تَعْبُدُونَ ( 92 ) አል አሹዐራዕ - Aya 92
ለእነሱም በሚባል ቀን «ትግገዟቸው የነበራችሁት የት ናቸው» አል አሹዐራዕ - Aya 92
مِن دُونِ اللَّهِ هَلْ يَنصُرُونَكُمْ أَوْ يَنتَصِرُونَ ( 93 ) አል አሹዐራዕ - Aya 93
«ከአላህ ሌላ ሲኾኑ ይረዱዋችኋልን ወይስ (ለራሳቸው) ይርረዳሉን» አል አሹዐራዕ - Aya 93
فَكُبْكِبُوا فِيهَا هُمْ وَالْغَاوُونَ ( 94 ) አል አሹዐራዕ - Aya 94
በውስጧም እነሱና ጠማሞቹ በፊቶቻቸው ተጥለው ይንከባለላሉ፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 94
وَجُنُودُ إِبْلِيسَ أَجْمَعُونَ ( 95 ) አል አሹዐራዕ - Aya 95
የሰይጣንም ሰራዊቶች መላውም (ይጣላሉ)፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 95
قَالُوا وَهُمْ فِيهَا يَخْتَصِمُونَ ( 96 ) አል አሹዐራዕ - Aya 96
እነርሱም በእርሷ ውስጥ የሚከራከሩ ኾነው ይላሉ፡- አል አሹዐራዕ - Aya 96
تَاللَّهِ إِن كُنَّا لَفِي ضَلَالٍ مُّبِينٍ ( 97 ) አል አሹዐራዕ - Aya 97
በአላህ እንምላለን፤ እኛ በግልጽ መሳሳት ውስጥ ነበርን፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 97
إِذْ نُسَوِّيكُم بِرَبِّ الْعَالَمِينَ ( 98 ) አል አሹዐራዕ - Aya 98
(ጣዖቶቹን) በዓለማት ጌታ ባስተካከልናችሁ ጊዜ፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 98
وَمَا أَضَلَّنَا إِلَّا الْمُجْرِمُونَ ( 99 ) አል አሹዐራዕ - Aya 99
አመጸኞቹም እንጅ ሌላ አላሳሳተንም፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 99
فَمَا لَنَا مِن شَافِعِينَ ( 100 ) አል አሹዐራዕ - Aya 100
ከአማላጆችም ለእኛ ምንም የለንም፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 100
وَلَا صَدِيقٍ حَمِيمٍ ( 101 ) አል አሹዐራዕ - Aya 101
አዛኝ ወዳጂም (የለንም)፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 101
فَلَوْ أَنَّ لَنَا كَرَّةً فَنَكُونَ مِنَ الْمُؤْمِنِينَ ( 102 ) አል አሹዐራዕ - Aya 102
ለእኛም አንዲት ጊዜ መመለስ በኖረችንና ከአማኞቹ በኾን እንመኛለን (ይላሉ)፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 102
إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَآيَةً ۖ وَمَا كَانَ أَكْثَرُهُم مُّؤْمِنِينَ ( 103 ) አል አሹዐራዕ - Aya 103
በዚህ ውስጥ አስደናቂ ግሳጼ አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም አማኞች አልነበሩም፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 103
وَإِنَّ رَبَّكَ لَهُوَ الْعَزِيزُ الرَّحِيمُ ( 104 ) አል አሹዐራዕ - Aya 104
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 104
كَذَّبَتْ قَوْمُ نُوحٍ الْمُرْسَلِينَ ( 105 ) አል አሹዐራዕ - Aya 105
የኑሕ ሕዝቦች መልክተኞችን አስተባበሉ፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 105
إِذْ قَالَ لَهُمْ أَخُوهُمْ نُوحٌ أَلَا تَتَّقُونَ ( 106 ) አል አሹዐራዕ - Aya 106
ወንድማቸው ኑሕ ለእነሱ ባላቸው ጊዜ «አትጠነቀቁምን አል አሹዐራዕ - Aya 106
إِنِّي لَكُمْ رَسُولٌ أَمِينٌ ( 107 ) አል አሹዐራዕ - Aya 107
«እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 107
فَاتَّقُوا اللَّهَ وَأَطِيعُونِ ( 108 ) አል አሹዐራዕ - Aya 108
«አላህንም ፍሩ ታዘዙኝም፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 108
وَمَا أَسْأَلُكُمْ عَلَيْهِ مِنْ أَجْرٍ ۖ إِنْ أَجْرِيَ إِلَّا عَلَىٰ رَبِّ الْعَالَمِينَ ( 109 ) አል አሹዐራዕ - Aya 109
«በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ አልጠይቃችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 109
فَاتَّقُوا اللَّهَ وَأَطِيعُونِ ( 110 ) አል አሹዐራዕ - Aya 110
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡» አል አሹዐራዕ - Aya 110
قَالُوا أَنُؤْمِنُ لَكَ وَاتَّبَعَكَ الْأَرْذَلُونَ ( 111 ) አል አሹዐራዕ - Aya 111
(እነርሱም) «ወራዶቹ የተከተሉህ ኾነህ ለአንተ እናምናለን» አሉት፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 111
قَالَ وَمَا عِلْمِي بِمَا كَانُوا يَعْمَلُونَ ( 112 ) አል አሹዐራዕ - Aya 112
(እርሱም) አላቸው «ይሠሩት በነበሩት ነገር ምን ዕውቀት አለኝ፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 112
إِنْ حِسَابُهُمْ إِلَّا عَلَىٰ رَبِّي ۖ لَوْ تَشْعُرُونَ ( 113 ) አል አሹዐራዕ - Aya 113
«ምርመራቸው በጌታዬ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡ ብታውቁ ኖሮ (ይህንን ትርረዱ ነበር)፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 113
وَمَا أَنَا بِطَارِدِ الْمُؤْمِنِينَ ( 114 ) አል አሹዐራዕ - Aya 114
«እኔም አማኞችን አባራሪ አይደለሁም፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 114
إِنْ أَنَا إِلَّا نَذِيرٌ مُّبِينٌ ( 115 ) አል አሹዐራዕ - Aya 115
«እኔ ግልጽ አስፈራሪ እንጅ ሌላ አይደለሁም፡፡» አል አሹዐራዕ - Aya 115
قَالُوا لَئِن لَّمْ تَنتَهِ يَا نُوحُ لَتَكُونَنَّ مِنَ الْمَرْجُومِينَ ( 116 ) አል አሹዐራዕ - Aya 116
«ኑሕ ሆይ! (ከምትለው) ባትከለከል በእርግጥ ከሚወገሩት ትኾናለህ» አሉት፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 116
قَالَ رَبِّ إِنَّ قَوْمِي كَذَّبُونِ ( 117 ) አል አሹዐራዕ - Aya 117
(እርሱም) አለ «ጌታዬ ሆይ! ሕዝቦቼ አስተባበሉኝ፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 117
فَافْتَحْ بَيْنِي وَبَيْنَهُمْ فَتْحًا وَنَجِّنِي وَمَن مَّعِيَ مِنَ الْمُؤْمِنِينَ ( 118 ) አል አሹዐራዕ - Aya 118
«በእኔና በእነርሱም መካከል (ተገቢ) ፍርድን ፍረድ፡፡ አድነኝም፡፡ ከእኔ ጋር ያሉትንም ምእምናን፡፡» አል አሹዐራዕ - Aya 118
فَأَنجَيْنَاهُ وَمَن مَّعَهُ فِي الْفُلْكِ الْمَشْحُونِ ( 119 ) አል አሹዐራዕ - Aya 119
እርሱንም ከእርሱ ጋር ያለውንም ሁሉ በተመላው መርከብ ውስጥ አዳን፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 119
ثُمَّ أَغْرَقْنَا بَعْدُ الْبَاقِينَ ( 120 ) አል አሹዐራዕ - Aya 120
ከዚያም በኋላ ቀሪዎቹን አሰጠምን፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 120
إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَآيَةً ۖ وَمَا كَانَ أَكْثَرُهُم مُّؤْمِنِينَ ( 121 ) አል አሹዐራዕ - Aya 121
በዚህ ውስጥ ታላቅ ግሳጼ አለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም አማኞች አልነበሩም፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 121
وَإِنَّ رَبَّكَ لَهُوَ الْعَزِيزُ الرَّحِيمُ ( 122 ) አል አሹዐራዕ - Aya 122
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 122
كَذَّبَتْ عَادٌ الْمُرْسَلِينَ ( 123 ) አል አሹዐራዕ - Aya 123
ዓድ መልክተኞችን አስተባበለች፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 123
إِذْ قَالَ لَهُمْ أَخُوهُمْ هُودٌ أَلَا تَتَّقُونَ ( 124 ) አል አሹዐራዕ - Aya 124
ወንድማቸው ሁድ ለነርሱ ባላቸው ጊዜ «አትጠነቀቁምን አል አሹዐራዕ - Aya 124
إِنِّي لَكُمْ رَسُولٌ أَمِينٌ ( 125 ) አል አሹዐራዕ - Aya 125
«እኔ ለናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 125
فَاتَّقُوا اللَّهَ وَأَطِيعُونِ ( 126 ) አል አሹዐራዕ - Aya 126
«አላህንም ፍሩ ታዘዙኝም፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 126
وَمَا أَسْأَلُكُمْ عَلَيْهِ مِنْ أَجْرٍ ۖ إِنْ أَجْرِيَ إِلَّا عَلَىٰ رَبِّ الْعَالَمِينَ ( 127 ) አል አሹዐራዕ - Aya 127
«በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ አለምናችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 127
أَتَبْنُونَ بِكُلِّ رِيعٍ آيَةً تَعْبَثُونَ ( 128 ) አል አሹዐራዕ - Aya 128
«የምትጫወቱ ኾናችሁ በከፍተኛ ስፍራ ሁሉ ላይ ምልክትን ትገነባላችሁን አል አሹዐራዕ - Aya 128
وَتَتَّخِذُونَ مَصَانِعَ لَعَلَّكُمْ تَخْلُدُونَ ( 129 ) አል አሹዐራዕ - Aya 129
«የውሃ ማጠራቀሚያዎችንና ሕንፃዎችንም ዘላለም መኖርን የምትከጅሉ ኾናችሁ ትሠራላችሁን አል አሹዐራዕ - Aya 129
وَإِذَا بَطَشْتُم بَطَشْتُمْ جَبَّارِينَ ( 130 ) አል አሹዐራዕ - Aya 130
«በቀጣችሁም ጊዜ ጨካኞች ኾናችሁ ትቀጣላችሁን አል አሹዐራዕ - Aya 130
فَاتَّقُوا اللَّهَ وَأَطِيعُونِ ( 131 ) አል አሹዐራዕ - Aya 131
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 131
وَاتَّقُوا الَّذِي أَمَدَّكُم بِمَا تَعْلَمُونَ ( 132 ) አል አሹዐራዕ - Aya 132
«ያንንም በምታውቁት (ጸጋ) ያጣቀማችሁን ፍሩ፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 132
أَمَدَّكُم بِأَنْعَامٍ وَبَنِينَ ( 133 ) አል አሹዐራዕ - Aya 133
«በእንስሳዎችና በልጆች ያጣቀማችሁን፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 133
وَجَنَّاتٍ وَعُيُونٍ ( 134 ) አል አሹዐራዕ - Aya 134
«በአትክልቶችና በምንጮችም፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 134
إِنِّي أَخَافُ عَلَيْكُمْ عَذَابَ يَوْمٍ عَظِيمٍ ( 135 ) አል አሹዐራዕ - Aya 135
«እኔ በእናንተ ላይ የታላቅን ቀን ቅጣት እፈራለሁና፡፡» አል አሹዐራዕ - Aya 135
قَالُوا سَوَاءٌ عَلَيْنَا أَوَعَظْتَ أَمْ لَمْ تَكُن مِّنَ الْوَاعِظِينَ ( 136 ) አል አሹዐራዕ - Aya 136
(እነርሱም) አሉ «ብትገስጽም ወይም ከገሳጮቹ ባትኾንም በእኛ ላይ እኩል ነው፤ (ያለንበትን አንለቅም)፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 136
إِنْ هَٰذَا إِلَّا خُلُقُ الْأَوَّلِينَ ( 137 ) አል አሹዐራዕ - Aya 137
«ይህ የፊተኞቹ ሰዎች ፀባይ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 137
وَمَا نَحْنُ بِمُعَذَّبِينَ ( 138 ) አል አሹዐራዕ - Aya 138
«እኛም የምንቅቀጣ አይደለንም» (አሉ)፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 138
فَكَذَّبُوهُ فَأَهْلَكْنَاهُمْ ۗ إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَآيَةً ۖ وَمَا كَانَ أَكْثَرُهُم مُّؤْمِنِينَ ( 139 ) አል አሹዐራዕ - Aya 139
አስተባበሉትም፡፡ አጠፋናቸውም፡፡ በዚህም ውስጥ እርግጠኛ ግሳጼ አለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም ምእመናን አልነበሩም፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 139
وَإِنَّ رَبَّكَ لَهُوَ الْعَزِيزُ الرَّحِيمُ ( 140 ) አል አሹዐራዕ - Aya 140
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 140
كَذَّبَتْ ثَمُودُ الْمُرْسَلِينَ ( 141 ) አል አሹዐራዕ - Aya 141
ሰሙድ መልክተኞችን አስተባበለች፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 141
إِذْ قَالَ لَهُمْ أَخُوهُمْ صَالِحٌ أَلَا تَتَّقُونَ ( 142 ) አል አሹዐራዕ - Aya 142
ወንድማቸው ሷሊህ ለእነርሱ ባላቸው ጊዜ «አትጠነቀቁምን አል አሹዐራዕ - Aya 142
إِنِّي لَكُمْ رَسُولٌ أَمِينٌ ( 143 ) አል አሹዐራዕ - Aya 143
«እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 143
فَاتَّقُوا اللَّهَ وَأَطِيعُونِ ( 144 ) አል አሹዐራዕ - Aya 144
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 144
وَمَا أَسْأَلُكُمْ عَلَيْهِ مِنْ أَجْرٍ ۖ إِنْ أَجْرِيَ إِلَّا عَلَىٰ رَبِّ الْعَالَمِينَ ( 145 ) አል አሹዐራዕ - Aya 145
«በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ አልለምናችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 145
أَتُتْرَكُونَ فِي مَا هَاهُنَا آمِنِينَ ( 146 ) አል አሹዐራዕ - Aya 146
«በዚያ እዚህ ባለው (ጸጋ) ውስጥ የረካችሁ ኾናችሁ ትተዋላችሁን አል አሹዐራዕ - Aya 146
فِي جَنَّاتٍ وَعُيُونٍ ( 147 ) አል አሹዐራዕ - Aya 147
«በአትክልቶችና በምንጮች ውስጥ፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 147
وَزُرُوعٍ وَنَخْلٍ طَلْعُهَا هَضِيمٌ ( 148 ) አል አሹዐራዕ - Aya 148
«በአዝመራዎችም ፍሬዋ የበሰለ በኾነች ዘንባባም፤ (ውስጥ ትተዋላችሁን) አል አሹዐራዕ - Aya 148
وَتَنْحِتُونَ مِنَ الْجِبَالِ بُيُوتًا فَارِهِينَ ( 149 ) አል አሹዐራዕ - Aya 149
«ብልሆች ኾናችሁ ከጋራዎች ቤቶችንም ትጠርባላችሁ፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 149
فَاتَّقُوا اللَّهَ وَأَطِيعُونِ ( 150 ) አል አሹዐራዕ - Aya 150
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 150
وَلَا تُطِيعُوا أَمْرَ الْمُسْرِفِينَ ( 151 ) አል አሹዐራዕ - Aya 151
«የወሰን አላፊዎችንም ትዕዛዝ አትከተሉ፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 151
الَّذِينَ يُفْسِدُونَ فِي الْأَرْضِ وَلَا يُصْلِحُونَ ( 152 ) አል አሹዐራዕ - Aya 152
«የእነዚያን በምድር ላይ የሚያጠፉትንና የማያበጁትን፡፡» አል አሹዐራዕ - Aya 152
قَالُوا إِنَّمَا أَنتَ مِنَ الْمُسَحَّرِينَ ( 153 ) አል አሹዐራዕ - Aya 153
(እነሱም) አሉ «አንተ በብዙ ከተደገመባቸው ሰዎች ብቻ ነህ፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 153
مَا أَنتَ إِلَّا بَشَرٌ مِّثْلُنَا فَأْتِ بِآيَةٍ إِن كُنتَ مِنَ الصَّادِقِينَ ( 154 ) አል አሹዐራዕ - Aya 154
«አንተ ብጤያችን ሰው እንጅ ሌላ አይደለህም፡፡ ከእውነተኞቹም እንደኾንክ ተዓምርን አምጣ፡፡» አል አሹዐራዕ - Aya 154
قَالَ هَٰذِهِ نَاقَةٌ لَّهَا شِرْبٌ وَلَكُمْ شِرْبُ يَوْمٍ مَّعْلُومٍ ( 155 ) አል አሹዐራዕ - Aya 155
(እርሱም) አለ «ይህች ግመል ናት፡፡ ለእርሷ የመጠጥ ፋንታ አላት፡፡ ለእናንተም የታወቀ ቀን ፋንታ አላችሁ፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 155
وَلَا تَمَسُّوهَا بِسُوءٍ فَيَأْخُذَكُمْ عَذَابُ يَوْمٍ عَظِيمٍ ( 156 ) አል አሹዐራዕ - Aya 156
«በክፉም አትንኳት፡፡ የታላቅ ቀን ቅጣት ይይዛችኋልና፡፡» አል አሹዐራዕ - Aya 156
فَعَقَرُوهَا فَأَصْبَحُوا نَادِمِينَ ( 157 ) አል አሹዐራዕ - Aya 157
ወጓትም፡፡ ወዲያውም ተጸጻቾች ኾነው አነጉ፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 157
فَأَخَذَهُمُ الْعَذَابُ ۗ إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَآيَةً ۖ وَمَا كَانَ أَكْثَرُهُم مُّؤْمِنِينَ ( 158 ) አል አሹዐራዕ - Aya 158
ቅጣቱም ያዛቸው፡፡ በዚህም ውስጥ ግሳፄ አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም ምእመናን አልነበሩም፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 158
وَإِنَّ رَبَّكَ لَهُوَ الْعَزِيزُ الرَّحِيمُ ( 159 ) አል አሹዐራዕ - Aya 159
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 159
كَذَّبَتْ قَوْمُ لُوطٍ الْمُرْسَلِينَ ( 160 ) አል አሹዐራዕ - Aya 160
የሉጥ ሕዝቦች መልክተኞችን አስተባባሉ፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 160
إِذْ قَالَ لَهُمْ أَخُوهُمْ لُوطٌ أَلَا تَتَّقُونَ ( 161 ) አል አሹዐራዕ - Aya 161
ወንድማቸው ሉጥ ለእነርሱ ባለ ጊዜ «አትጠነቀቁምን አል አሹዐራዕ - Aya 161
إِنِّي لَكُمْ رَسُولٌ أَمِينٌ ( 162 ) አል አሹዐራዕ - Aya 162
«እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 162
فَاتَّقُوا اللَّهَ وَأَطِيعُونِ ( 163 ) አል አሹዐራዕ - Aya 163
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 163
وَمَا أَسْأَلُكُمْ عَلَيْهِ مِنْ أَجْرٍ ۖ إِنْ أَجْرِيَ إِلَّا عَلَىٰ رَبِّ الْعَالَمِينَ ( 164 ) አል አሹዐራዕ - Aya 164
«በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ አልለምናችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 164
أَتَأْتُونَ الذُّكْرَانَ مِنَ الْعَالَمِينَ ( 165 ) አል አሹዐራዕ - Aya 165
«ከዓለማት ሰዎች ወንዶችን ትመጣላችሁን አል አሹዐራዕ - Aya 165
وَتَذَرُونَ مَا خَلَقَ لَكُمْ رَبُّكُم مِّنْ أَزْوَاجِكُم ۚ بَلْ أَنتُمْ قَوْمٌ عَادُونَ ( 166 ) አል አሹዐራዕ - Aya 166
«ከሚስቶቻችሁም ጌታችሁ ለናንተ የፈጠረላችሁን ትተዋላችሁን በእውነቱ እናንተ ወሰን አላፊዎች ሕዝቦ ናችሁ፡፡» አል አሹዐራዕ - Aya 166
قَالُوا لَئِن لَّمْ تَنتَهِ يَا لُوطُ لَتَكُونَنَّ مِنَ الْمُخْرَجِينَ ( 167 ) አል አሹዐራዕ - Aya 167
(እነርሱም) አሉ «ሉጥ ሆይ! ባትከለከል በእርግጥ (ከአገር) ከሚወጡት ትኾናለህ፡፡» አል አሹዐራዕ - Aya 167
قَالَ إِنِّي لِعَمَلِكُم مِّنَ الْقَالِينَ ( 168 ) አል አሹዐራዕ - Aya 168
(እርሱም) አለ «እኔ ሥራችሁን ከሚጠሉት ሰዎች ነኝ፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 168
رَبِّ نَجِّنِي وَأَهْلِي مِمَّا يَعْمَلُونَ ( 169 ) አል አሹዐራዕ - Aya 169
«ጌታዬ ሆይ! እኔንም ቤተሰቦቼንም ከሚሠሩት ሥራ (ቅጣት) አድነን፡፡» አል አሹዐራዕ - Aya 169
فَنَجَّيْنَاهُ وَأَهْلَهُ أَجْمَعِينَ ( 170 ) አል አሹዐራዕ - Aya 170
እርሱንም ቤተሰቦቹንም በጠቅላላ አዳንናቸው፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 170
إِلَّا عَجُوزًا فِي الْغَابِرِينَ ( 171 ) አል አሹዐራዕ - Aya 171
በቀሪዎቹ ውስጥ የኾነች አሮጊት ብቻ ስትቀር (እርሷ ጠፋች)፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 171
ثُمَّ دَمَّرْنَا الْآخَرِينَ ( 172 ) አል አሹዐራዕ - Aya 172
ከዚያም ሌሎቹን አጠፋን፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 172
وَأَمْطَرْنَا عَلَيْهِم مَّطَرًا ۖ فَسَاءَ مَطَرُ الْمُنذَرِينَ ( 173 ) አል አሹዐራዕ - Aya 173
በእነሱም ላይ (የድንጋይን) ዝናምን አዘነምንባቸው፡፡ የተስፈራሪዎቹም ዝናም (ምንኛ) ከፋ፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 173
إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَآيَةً ۖ وَمَا كَانَ أَكْثَرُهُم مُّؤْمِنِينَ ( 174 ) አል አሹዐራዕ - Aya 174
በዚህ ውስጥ አስደናቂ ተዓምር አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም ምእመናን አልነበሩም፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 174
وَإِنَّ رَبَّكَ لَهُوَ الْعَزِيزُ الرَّحِيمُ ( 175 ) አል አሹዐራዕ - Aya 175
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 175
كَذَّبَ أَصْحَابُ الْأَيْكَةِ الْمُرْسَلِينَ ( 176 ) አል አሹዐራዕ - Aya 176
የአይከት ሰዎች መልክተኞችን አስተባበሉ፤ አል አሹዐራዕ - Aya 176
إِذْ قَالَ لَهُمْ شُعَيْبٌ أَلَا تَتَّقُونَ ( 177 ) አል አሹዐራዕ - Aya 177
ሹዕይብ ለእነርሱ ባላቸው ጊዜ «አትጠነቀቁምን አል አሹዐራዕ - Aya 177
إِنِّي لَكُمْ رَسُولٌ أَمِينٌ ( 178 ) አል አሹዐራዕ - Aya 178
«እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 178
فَاتَّقُوا اللَّهَ وَأَطِيعُونِ ( 179 ) አል አሹዐራዕ - Aya 179
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 179
وَمَا أَسْأَلُكُمْ عَلَيْهِ مِنْ أَجْرٍ ۖ إِنْ أَجْرِيَ إِلَّا عَلَىٰ رَبِّ الْعَالَمِينَ ( 180 ) አል አሹዐራዕ - Aya 180
«በርሱም ላይ ምንም ዋጋ አልጠይቃችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 180
أَوْفُوا الْكَيْلَ وَلَا تَكُونُوا مِنَ الْمُخْسِرِينَ ( 181 ) አል አሹዐራዕ - Aya 181
«ስፍርን ሙሉ፡፡ ከአጉዳዮቹም አትኹኑ፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 181
وَزِنُوا بِالْقِسْطَاسِ الْمُسْتَقِيمِ ( 182 ) አል አሹዐራዕ - Aya 182
«በትክክለኛ ሚዛንም መዝኑ፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 182
وَلَا تَبْخَسُوا النَّاسَ أَشْيَاءَهُمْ وَلَا تَعْثَوْا فِي الْأَرْضِ مُفْسِدِينَ ( 183 ) አል አሹዐራዕ - Aya 183
«ሰዎችንም ነገሮቻቸውን አታጉድሉባቸው፡፡ በምድርም ላይ አጥፊዎች ኾናችሁ አታበላሹ፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 183
وَاتَّقُوا الَّذِي خَلَقَكُمْ وَالْجِبِلَّةَ الْأَوَّلِينَ ( 184 ) አል አሹዐራዕ - Aya 184
«ያንንም የፈጠራችሁን የቀድሞዎቹንም ፍጡሮች (የፈጠረውን) ፍሩ፡፡» አል አሹዐራዕ - Aya 184
قَالُوا إِنَّمَا أَنتَ مِنَ الْمُسَحَّرِينَ ( 185 ) አል አሹዐራዕ - Aya 185
አሉ «አንተ በብዛት ከተደገመባቸው ሰዎች ነህ፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 185
وَمَا أَنتَ إِلَّا بَشَرٌ مِّثْلُنَا وَإِن نَّظُنُّكَ لَمِنَ الْكَاذِبِينَ ( 186 ) አል አሹዐራዕ - Aya 186
«አንተም ብጤያችን ሰው እንጅ ሌላ አይደለህም፡፡ እነሆ ከውሸታሞች ነህ ብለን እንጠረጥርሃለን፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 186
فَأَسْقِطْ عَلَيْنَا كِسَفًا مِّنَ السَّمَاءِ إِن كُنتَ مِنَ الصَّادِقِينَ ( 187 ) አል አሹዐራዕ - Aya 187
«ከእውነተኞቹም እንደኾንክ በእኛ ላይ ከሰማይ ቁራጭን ጣልብን፡፡» አል አሹዐራዕ - Aya 187
قَالَ رَبِّي أَعْلَمُ بِمَا تَعْمَلُونَ ( 188 ) አል አሹዐራዕ - Aya 188
«ጌታዬ የምትሠሩትን ሁሉ ዐዋቂ ነው፤» አላቸው፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 188
فَكَذَّبُوهُ فَأَخَذَهُمْ عَذَابُ يَوْمِ الظُّلَّةِ ۚ إِنَّهُ كَانَ عَذَابَ يَوْمٍ عَظِيمٍ ( 189 ) አል አሹዐራዕ - Aya 189
አስተባበሉትም፡፡ የጥላይቷ ቀን ቅጣትም ያዛቸው፡፡ እርሱ የከባድ ቀን ቅጣት ነበርና፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 189
إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَآيَةً ۖ وَمَا كَانَ أَكْثَرُهُم مُّؤْمِنِينَ ( 190 ) አል አሹዐራዕ - Aya 190
በዚህ ውስጥ አስደናቂ ተዓምር አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም ምእምናን አልነበሩም፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 190
وَإِنَّ رَبَّكَ لَهُوَ الْعَزِيزُ الرَّحِيمُ ( 191 ) አል አሹዐራዕ - Aya 191
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 191
وَإِنَّهُ لَتَنزِيلُ رَبِّ الْعَالَمِينَ ( 192 ) አል አሹዐራዕ - Aya 192
እርሱም (ቁርኣን) በእርግጥ ከዓለማት ጌታ የተወረደ ነው፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 192
نَزَلَ بِهِ الرُّوحُ الْأَمِينُ ( 193 ) አል አሹዐራዕ - Aya 193
እርሱን ታማኙ መንፈስ (ጂብሪል) አወረደው፤ አል አሹዐራዕ - Aya 193
عَلَىٰ قَلْبِكَ لِتَكُونَ مِنَ الْمُنذِرِينَ ( 194 ) አል አሹዐራዕ - Aya 194
ከአስፈራሪዎቹ (ነቢያት) ትኾን ዘንድ በልብህ ላይ (አወረደው)፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 194
بِلِسَانٍ عَرَبِيٍّ مُّبِينٍ ( 195 ) አል አሹዐራዕ - Aya 195
ግልጽ በኾነ ዐረብኛ ቋንቋ፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 195
وَإِنَّهُ لَفِي زُبُرِ الْأَوَّلِينَ ( 196 ) አል አሹዐራዕ - Aya 196
እርሱም (ቁርኣን) በቀድሞዎቹ መጻሐፍት ውስጥ (የተወሳ ነው)፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 196
أَوَلَمْ يَكُن لَّهُمْ آيَةً أَن يَعْلَمَهُ عُلَمَاءُ بَنِي إِسْرَائِيلَ ( 197 ) አል አሹዐራዕ - Aya 197
የእስራኤል ልጆች ሊቃውንት የሚያውቁት መኾኑ ለእነርሱ (ለመካ ከሓዲዎች) ምልክት አይኾናቸውምን አል አሹዐራዕ - Aya 197
وَلَوْ نَزَّلْنَاهُ عَلَىٰ بَعْضِ الْأَعْجَمِينَ ( 198 ) አል አሹዐራዕ - Aya 198
ከአዕጀሞች ባንዱ ላይ ባወረድነውም ኖሮ፤ አል አሹዐራዕ - Aya 198
فَقَرَأَهُ عَلَيْهِم مَّا كَانُوا بِهِ مُؤْمِنِينَ ( 199 ) አል አሹዐራዕ - Aya 199
በእነርሱ ላይ ባነበበውም በእርሱ አማኞች አይኾኑም ነበር፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 199
كَذَٰلِكَ سَلَكْنَاهُ فِي قُلُوبِ الْمُجْرِمِينَ ( 200 ) አል አሹዐራዕ - Aya 200
እንደዚሁ (ማስተባበልን) በተንኮለኞች ልቦች ውስጥ አስገባነው፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 200
لَا يُؤْمِنُونَ بِهِ حَتَّىٰ يَرَوُا الْعَذَابَ الْأَلِيمَ ( 201 ) አል አሹዐራዕ - Aya 201
አሳማሚ ቅጣትን እስከሚያዩ ድረስ በእርሱ አያምኑም፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 201
فَيَأْتِيَهُم بَغْتَةً وَهُمْ لَا يَشْعُرُونَ ( 202 ) አል አሹዐራዕ - Aya 202
እነርሱ የማያውቁ ሲኾኑ (ቅጣቱ) ድንገት እስከሚመጣባቸውም ድረስ (አያምኑም)፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 202
فَيَقُولُوا هَلْ نَحْنُ مُنظَرُونَ ( 203 ) አል አሹዐራዕ - Aya 203
(በመጣባቸው ጊዜ) «እኛ የምንቆይ ነን» እስከሚሉም (አያምኑም)፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 203
أَفَبِعَذَابِنَا يَسْتَعْجِلُونَ ( 204 ) አል አሹዐራዕ - Aya 204
በቅጣታችን ያቻኩላሉን አል አሹዐራዕ - Aya 204
أَفَرَأَيْتَ إِن مَّتَّعْنَاهُمْ سِنِينَ ( 205 ) አል አሹዐራዕ - Aya 205
አየህን ብዙ ዓመታትን ብናጣቅማቸው፤ አል አሹዐራዕ - Aya 205
ثُمَّ جَاءَهُم مَّا كَانُوا يُوعَدُونَ ( 206 ) አል አሹዐራዕ - Aya 206
ከዚያም ያ ይስፈራሩበት የነበሩት ቢመጣባቸው፤ አል አሹዐራዕ - Aya 206
مَا أَغْنَىٰ عَنْهُم مَّا كَانُوا يُمَتَّعُونَ ( 207 ) አል አሹዐራዕ - Aya 207
ይጣቀሙበት የነበሩት ሁሉ ከእነሱ ምንም አያብቃቃቸውም፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 207
وَمَا أَهْلَكْنَا مِن قَرْيَةٍ إِلَّا لَهَا مُنذِرُونَ ( 208 ) አል አሹዐራዕ - Aya 208
አንዲትንም ከተማ ለእርሷ አስፈራሪዎች ያሏት (እና ያስተባበለች) ኾና እንጅ አላጠፋንም፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 208
ذِكْرَىٰ وَمَا كُنَّا ظَالِمِينَ ( 209 ) አል አሹዐራዕ - Aya 209
(ይህች) ግሳፄ ናት፡፡ በዳዮችም አልነበርንም፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 209
وَمَا تَنَزَّلَتْ بِهِ الشَّيَاطِينُ ( 210 ) አል አሹዐራዕ - Aya 210
ሰይጣናትም እርሱን (ቁርኣንን) አላወረዱትም፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 210
وَمَا يَنبَغِي لَهُمْ وَمَا يَسْتَطِيعُونَ ( 211 ) አል አሹዐራዕ - Aya 211
ለእነርሱም አይገባቸውም፤ አይችሉምም፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 211
إِنَّهُمْ عَنِ السَّمْعِ لَمَعْزُولُونَ ( 212 ) አል አሹዐራዕ - Aya 212
እነርሱ (የመላእክትን ንግግር) ከመስማት ተከለከሉ ናቸው፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 212
فَلَا تَدْعُ مَعَ اللَّهِ إِلَٰهًا آخَرَ فَتَكُونَ مِنَ الْمُعَذَّبِينَ ( 213 ) አል አሹዐራዕ - Aya 213
ከአላህም ጋር ሌላን አምላክ አትግገዛ፤ ከሚቀጡት ትኾናለህና፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 213
وَأَنذِرْ عَشِيرَتَكَ الْأَقْرَبِينَ ( 214 ) አል አሹዐራዕ - Aya 214
ቅርቦች ዘመዶችህንም አስጠንቅቅ፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 214
وَاخْفِضْ جَنَاحَكَ لِمَنِ اتَّبَعَكَ مِنَ الْمُؤْمِنِينَ ( 215 ) አል አሹዐራዕ - Aya 215
ከምእምናንም ለተከተሉህ ሰዎች ክንፍህን ዝቅ አድርግ፤ (ልዝብ ኹን)፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 215
فَإِنْ عَصَوْكَ فَقُلْ إِنِّي بَرِيءٌ مِّمَّا تَعْمَلُونَ ( 216 ) አል አሹዐራዕ - Aya 216
«እንቢ» ቢሉህም «እኔ ከምትሠሩት ንጹሕ ነኝ» በላቸው፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 216
وَتَوَكَّلْ عَلَى الْعَزِيزِ الرَّحِيمِ ( 217 ) አል አሹዐራዕ - Aya 217
አሸናፊ አዛኝ በኾነው (ጌታህ) ላይም ተጠጋ፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 217
الَّذِي يَرَاكَ حِينَ تَقُومُ ( 218 ) አል አሹዐራዕ - Aya 218
በዚያ ለሶላት በምትቆም ጊዜ በሚያይህ፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 218
وَتَقَلُّبَكَ فِي السَّاجِدِينَ ( 219 ) አል አሹዐራዕ - Aya 219
በሰጋጆች ውስጥ መዘዋወርህንም (በሚያየው ጌታህ ላይ ተጠጋ)፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 219
إِنَّهُ هُوَ السَّمِيعُ الْعَلِيمُ ( 220 ) አል አሹዐራዕ - Aya 220
እነሆ እርሱ ሰሚው ዐዋቂው ነውና፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 220
هَلْ أُنَبِّئُكُمْ عَلَىٰ مَن تَنَزَّلُ الشَّيَاطِينُ ( 221 ) አል አሹዐራዕ - Aya 221
ሰይጣናት በማን ላይ እንደሚወርዱ ልንገራችሁን አል አሹዐራዕ - Aya 221
تَنَزَّلُ عَلَىٰ كُلِّ أَفَّاكٍ أَثِيمٍ ( 222 ) አል አሹዐራዕ - Aya 222
በውሸታም ኀጢአተኛ ሁሉ ላይ ይወርዳሉ፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 222
يُلْقُونَ السَّمْعَ وَأَكْثَرُهُمْ كَاذِبُونَ ( 223 ) አል አሹዐራዕ - Aya 223
የሰሙትን (ወደ ጠንቋዮች) ይጥላሉ፡፡ አብዛኞቻቸውም ውሸታሞች ናቸው፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 223
وَالشُّعَرَاءُ يَتَّبِعُهُمُ الْغَاوُونَ ( 224 ) አል አሹዐራዕ - Aya 224
ባለ ቅኔዎችንም ጠማማዎቹ ይከተሉዋቸዋል፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 224
أَلَمْ تَرَ أَنَّهُمْ فِي كُلِّ وَادٍ يَهِيمُونَ ( 225 ) አል አሹዐራዕ - Aya 225
እነርሱ በ(ንግግር) ሸለቆ ሁሉ የሚዋልሉ መኾናቸውን አታይምን አል አሹዐራዕ - Aya 225
وَأَنَّهُمْ يَقُولُونَ مَا لَا يَفْعَلُونَ ( 226 ) አል አሹዐራዕ - Aya 226
እነሱም የማይሠሩትን ነገር የሚናገሩ መኾናቸውን (አታይምን)፤ አል አሹዐራዕ - Aya 226
إِلَّا الَّذِينَ آمَنُوا وَعَمِلُوا الصَّالِحَاتِ وَذَكَرُوا اللَّهَ كَثِيرًا وَانتَصَرُوا مِن بَعْدِ مَا ظُلِمُوا ۗ وَسَيَعْلَمُ الَّذِينَ ظَلَمُوا أَيَّ مُنقَلَبٍ يَنقَلِبُونَ ( 227 ) አል አሹዐራዕ - Aya 227
እነዚያ ያመኑና መልካም ሥራዎችን የሠሩ አላህንም በብዛት ያወሱ ከተበደሉም በኋላ (በቅኔ) የተከላከሉ ሲቀሩ፤ (እነርሱ አይወቀሱም)፡፡ እነዚያም የበደሉ (ከሞቱ በኋላ) እንዴት ያለን መመለስ እንደሚመለሱ በእርግጥ ያውቃሉ፡፡ አል አሹዐራዕ - Aya 227
Facebook Twitter Google+ Pinterest Reddit StumbleUpon Linkedin Tumblr Google Bookmarks Email

Select Translation

Select surah