Surah አል ረሕማን

አማርኛ Muhammad Sadiq & Sani Habib

Surah አል ረሕማን - Aya count 78
Facebook Twitter Google+ Pinterest Reddit StumbleUpon Linkedin Tumblr Google Bookmarks Email
الرَّحْمَٰنُ ( 1 ) አል ረሕማን - Aya 1
አል-ረሕማን፤ አል ረሕማን - Aya 1
عَلَّمَ الْقُرْآنَ ( 2 ) አል ረሕማን - Aya 2
ቁርኣንን አስተማረ፡፡ አል ረሕማን - Aya 2
خَلَقَ الْإِنسَانَ ( 3 ) አል ረሕማን - Aya 3
ሰውን ፈጠረ፡፡ አል ረሕማን - Aya 3
عَلَّمَهُ الْبَيَانَ ( 4 ) አል ረሕማን - Aya 4
መናገርን አስተማረው፡፡ አል ረሕማን - Aya 4
الشَّمْسُ وَالْقَمَرُ بِحُسْبَانٍ ( 5 ) አል ረሕማን - Aya 5
ፀሐይና ጨረቃ በተወሰነ ልክ (ይኼዳሉ)፡፡ አል ረሕማን - Aya 5
وَالنَّجْمُ وَالشَّجَرُ يَسْجُدَانِ ( 6 ) አል ረሕማን - Aya 6
ሐረግና ዛፍም (ለእርሱ) ይሰግዳሉ፡፡ አል ረሕማን - Aya 6
وَالسَّمَاءَ رَفَعَهَا وَوَضَعَ الْمِيزَانَ ( 7 ) አል ረሕማን - Aya 7
ሰማይንም አጓናት፡፡ ትክክለኛነትንም ደነገገ፡፡ አል ረሕማን - Aya 7
أَلَّا تَطْغَوْا فِي الْمِيزَانِ ( 8 ) አል ረሕማን - Aya 8
በሚዛን (ስትመዝኑ) እንዳትበድሉ፡፡ አል ረሕማን - Aya 8
وَأَقِيمُوا الْوَزْنَ بِالْقِسْطِ وَلَا تُخْسِرُوا الْمِيزَانَ ( 9 ) አል ረሕማን - Aya 9
መመዘንንም በትክክል መዝኑ፡፡ ተመዛኙንም አታጉድሉ፡፡ አል ረሕማን - Aya 9
وَالْأَرْضَ وَضَعَهَا لِلْأَنَامِ ( 10 ) አል ረሕማን - Aya 10
ምድርንም ለፍጡሩ አደላደላት፡፡ አል ረሕማን - Aya 10
فِيهَا فَاكِهَةٌ وَالنَّخْلُ ذَاتُ الْأَكْمَامِ ( 11 ) አል ረሕማን - Aya 11
በውስጧ እሸት ባለ ሺፋኖች የኾኑ ዘንባባዎችም ያሉባት ስትኾን፡፡ አል ረሕማን - Aya 11
وَالْحَبُّ ذُو الْعَصْفِ وَالرَّيْحَانُ ( 12 ) አል ረሕማን - Aya 12
የገለባ ባለቤት የኾነ ቅንጣትም፡፡ ባለ መልካም መዐዛ ቅጠሎችም (ያሉባት ስትኾን)፡፡ አል ረሕማን - Aya 12
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ( 13 ) አል ረሕማን - Aya 13
(ሰዎችና ጋኔኖች ሆይ!) ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ? አል ረሕማን - Aya 13
خَلَقَ الْإِنسَانَ مِن صَلْصَالٍ كَالْفَخَّارِ ( 14 ) አል ረሕማን - Aya 14
ሰውን እንደ ሸክላ ከሚቅጨለጨል ደረቅ ጭቃ ፈጠረው፡፡ አል ረሕማን - Aya 14
وَخَلَقَ الْجَانَّ مِن مَّارِجٍ مِّن نَّارٍ ( 15 ) አል ረሕማን - Aya 15
ጃንንም ከእሳት ከኾነ ነበልባል ፈጠረው፡፡ አል ረሕማን - Aya 15
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ( 16 ) አል ረሕማን - Aya 16
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ? አል ረሕማን - Aya 16
رَبُّ الْمَشْرِقَيْنِ وَرَبُّ الْمَغْرِبَيْنِ ( 17 ) አል ረሕማን - Aya 17
የሁለቱ ምሥራቆች ጌታ፤ የሁለቱ ምዕራቦችም ጌታ ነው፡፡ አል ረሕማን - Aya 17
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ( 18 ) አል ረሕማን - Aya 18
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ? አል ረሕማን - Aya 18
مَرَجَ الْبَحْرَيْنِ يَلْتَقِيَانِ ( 19 ) አል ረሕማን - Aya 19
ሁለቱን ባሕሮች የሚገናኙ ሲኾኑ ለቀቃቸው፡፡ አል ረሕማን - Aya 19
بَيْنَهُمَا بَرْزَخٌ لَّا يَبْغِيَانِ ( 20 ) አል ረሕማን - Aya 20
(እንዳይዋሐዱ) በመካከላቸው ጋራጅ አልለ፡፡ (አንዱ ባንዱ ላይ) ወሰን አያልፉም፡፡ አል ረሕማን - Aya 20
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ( 21 ) አል ረሕማን - Aya 21
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታሰተባብላላችሁ?› አል ረሕማን - Aya 21
يَخْرُجُ مِنْهُمَا اللُّؤْلُؤُ وَالْمَرْجَانُ ( 22 ) አል ረሕማን - Aya 22
ሉልና መርጃን ከሁለቱ ይወጣል፡፡ አል ረሕማን - Aya 22
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ( 23 ) አል ረሕማን - Aya 23
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ? አል ረሕማን - Aya 23
وَلَهُ الْجَوَارِ الْمُنشَآتُ فِي الْبَحْرِ كَالْأَعْلَامِ ( 24 ) አል ረሕማን - Aya 24
እንደ ጋራዎች ኾነው በባሕር ውስጥ የተሠሩት ተንሻለዮቹም (ታንኳዎች) የእርሱ ናቸው፡፡ አል ረሕማን - Aya 24
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ( 25 ) አል ረሕማን - Aya 25
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ? አል ረሕማን - Aya 25
كُلُّ مَنْ عَلَيْهَا فَانٍ ( 26 ) አል ረሕማን - Aya 26
በእርሷ (በምድር) ላይ ያለው ሁሉ ጠፊ ነው፡፡ አል ረሕማን - Aya 26
وَيَبْقَىٰ وَجْهُ رَبِّكَ ذُو الْجَلَالِ وَالْإِكْرَامِ ( 27 ) አል ረሕማን - Aya 27
የልቅናና የልግሥና ባለቤት የኾነው የጌታህ ፊትም ይቀራል፡፡ (አይጠፋም)፡፡ አል ረሕማን - Aya 27
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ( 28 ) አል ረሕማን - Aya 28
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ? አል ረሕማን - Aya 28
يَسْأَلُهُ مَن فِي السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ ۚ كُلَّ يَوْمٍ هُوَ فِي شَأْنٍ ( 29 ) አል ረሕማን - Aya 29
በሰማያትና በምድር ውስጥ ያሉት ሁሉ ይለምኑታል፡፡ በየቀኑ ሁሉ እርሱ በሥራ ላይ ነው፡፡ አል ረሕማን - Aya 29
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ( 30 ) አል ረሕማን - Aya 30
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታሰተባብላላችሁ?› አል ረሕማን - Aya 30
سَنَفْرُغُ لَكُمْ أَيُّهَ الثَّقَلَانِ ( 31 ) አል ረሕማን - Aya 31
እናንተ ሁለት ከባዶች (ሰዎችና ጋኔኖች) ሆይ! ለእናንተ (መቆጣጠር) በእርግጥ እናስባለን፡፡ አል ረሕማን - Aya 31
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ( 32 ) አል ረሕማን - Aya 32
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ? አል ረሕማን - Aya 32
يَا مَعْشَرَ الْجِنِّ وَالْإِنسِ إِنِ اسْتَطَعْتُمْ أَن تَنفُذُوا مِنْ أَقْطَارِ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ فَانفُذُوا ۚ لَا تَنفُذُونَ إِلَّا بِسُلْطَانٍ ( 33 ) አል ረሕማን - Aya 33
የጋኔንና የሰው ጭፍሮች ሆይ! ከሰማያትና ከምድር ቀበሌዎች መውጣትን ብትችሉ ውጡ፡፡ በስልጣን እንጅ አትወጡም፡፡ (ግን ስልጣን የላችሁም) አል ረሕማን - Aya 33
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ( 34 ) አል ረሕማን - Aya 34
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ? አል ረሕማን - Aya 34
يُرْسَلُ عَلَيْكُمَا شُوَاظٌ مِّن نَّارٍ وَنُحَاسٌ فَلَا تَنتَصِرَانِ ( 35 ) አል ረሕማን - Aya 35
በሁለታችሁም ላይ ከእሳት ነበልባል፣ ጭስም ይላክባችኋል፡፡ (ሁለታችሁም) አትርረዱምም፡፡ አል ረሕማን - Aya 35
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ( 36 ) አል ረሕማን - Aya 36
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ? አል ረሕማን - Aya 36
فَإِذَا انشَقَّتِ السَّمَاءُ فَكَانَتْ وَرْدَةً كَالدِّهَانِ ( 37 ) አል ረሕማን - Aya 37
ሰማይም በተሰነጠቀችና እንደ ጽጌረዳ፣ እንደታረበ ቆዳ በኾነች ጊዜ፤ (ጭንቁን ምን አበረታው)፡፡ አል ረሕማን - Aya 37
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ( 38 ) አል ረሕማን - Aya 38
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ? አል ረሕማን - Aya 38
فَيَوْمَئِذٍ لَّا يُسْأَلُ عَن ذَنبِهِ إِنسٌ وَلَا جَانٌّ ( 39 ) አል ረሕማን - Aya 39
በዚያም ቀን ሰውም ጃንም ከኃጢኣቱ ገና አይጠየቅም፡፡ አል ረሕማን - Aya 39
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ( 40 ) አል ረሕማን - Aya 40
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ? አል ረሕማን - Aya 40
يُعْرَفُ الْمُجْرِمُونَ بِسِيمَاهُمْ فَيُؤْخَذُ بِالنَّوَاصِي وَالْأَقْدَامِ ( 41 ) አል ረሕማን - Aya 41
ከሓዲዎች በምልክታቸው ይታወቃሉ፡፡ አናቶቻቸውንና ጫማዎቻቸውንም ይያዛሉ፡፡ አል ረሕማን - Aya 41
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ( 42 ) አል ረሕማን - Aya 42
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ፡፡ አል ረሕማን - Aya 42
هَٰذِهِ جَهَنَّمُ الَّتِي يُكَذِّبُ بِهَا الْمُجْرِمُونَ ( 43 ) አል ረሕማን - Aya 43
ይህቺ ያቺ አመጸኞች በእርሷ ያስተባብሉባት የነበረችው ገሀነም ናት (ይባላሉ)፡፡ አል ረሕማን - Aya 43
يَطُوفُونَ بَيْنَهَا وَبَيْنَ حَمِيمٍ آنٍ ( 44 ) አል ረሕማን - Aya 44
በእርሷና በጣም ሞቃት በኾነ ፍል ውሃ መካከል ይመላለሳሉ፡፡ አል ረሕማን - Aya 44
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ( 45 ) አል ረሕማን - Aya 45
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ? አል ረሕማን - Aya 45
وَلِمَنْ خَافَ مَقَامَ رَبِّهِ جَنَّتَانِ ( 46 ) አል ረሕማን - Aya 46
በጌታውም ፊት መቆምን ለፈራ ሰው ሁለት ገነቶች አልሉት፡፡ አል ረሕማን - Aya 46
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ( 47 ) አል ረሕማን - Aya 47
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ? አል ረሕማን - Aya 47
ذَوَاتَا أَفْنَانٍ ( 48 ) አል ረሕማን - Aya 48
የቀንዘሎች ባለ ቤቶች የኾኑ (ገነቶች አልሉት)፡፡ አል ረሕማን - Aya 48
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ( 49 ) አል ረሕማን - Aya 49
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ? አል ረሕማን - Aya 49
فِيهِمَا عَيْنَانِ تَجْرِيَانِ ( 50 ) አል ረሕማን - Aya 50
በሁለቱ ውስጥ የሚፈስሱ ሁለት ምንጮች አልሉ፡፡ አል ረሕማን - Aya 50
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ( 51 ) አል ረሕማን - Aya 51
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ? አል ረሕማን - Aya 51
فِيهِمَا مِن كُلِّ فَاكِهَةٍ زَوْجَانِ ( 52 ) አል ረሕማን - Aya 52
በሁለቱ ውስጥ ከፍራፍሬዎች ሁሉ ሁለት ዓይነቶች (እርጥብና ደረቅ) አልሉ፡፡ አል ረሕማን - Aya 52
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ( 53 ) አል ረሕማን - Aya 53
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ? አል ረሕማን - Aya 53
مُتَّكِئِينَ عَلَىٰ فُرُشٍ بَطَائِنُهَا مِنْ إِسْتَبْرَقٍ ۚ وَجَنَى الْجَنَّتَيْنِ دَانٍ ( 54 ) አል ረሕማን - Aya 54
የውስጥ ጉስጉሳቸው ከወፍራም ሐር በኾኑ ምንጣፎች ላይ የተመቻቹ ሲኾኑ (ይንፈላሰሳሉ)፡፡ የሁለቱም ገነቶች ፍሬ (ለለቃሚ) ቅርብ ነው፡፡ አል ረሕማን - Aya 54
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ( 55 ) አል ረሕማን - Aya 55
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ? አል ረሕማን - Aya 55
فِيهِنَّ قَاصِرَاتُ الطَّرْفِ لَمْ يَطْمِثْهُنَّ إِنسٌ قَبْلَهُمْ وَلَا جَانٌّ ( 56 ) አል ረሕማን - Aya 56
በውስጣቸው ከበፊታቸው (ከባሎቻቸው በፊት) ሰውም ጃንም ያልገሰሳቸው ዓይኖቻቸውን (በባሎቻቸው ላይ) አሳጣሪዎች (ሴቶች) አልሉ፡፡ አል ረሕማን - Aya 56
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ( 57 ) አል ረሕማን - Aya 57
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ? አል ረሕማን - Aya 57
كَأَنَّهُنَّ الْيَاقُوتُ وَالْمَرْجَانُ ( 58 ) አል ረሕማን - Aya 58
ልክ ያቁትና መርጃን ይመስላሉ፡፡ አል ረሕማን - Aya 58
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ( 59 ) አል ረሕማን - Aya 59
ከጌታችሁም ጸጋዎቸ በየትኛው ታስተባብላላችሁ? አል ረሕማን - Aya 59
هَلْ جَزَاءُ الْإِحْسَانِ إِلَّا الْإِحْسَانُ ( 60 ) አል ረሕማን - Aya 60
የበጎ ሥራ ዋጋ በጎ እንጅ ሌላ ነውን? አል ረሕማን - Aya 60
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ( 61 ) አል ረሕማን - Aya 61
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ? አል ረሕማን - Aya 61
وَمِن دُونِهِمَا جَنَّتَانِ ( 62 ) አል ረሕማን - Aya 62
ከሁለቱ ገነቶችም ሌላ ሁለት ገነቶች አልሉ፡፡ አል ረሕማን - Aya 62
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ( 63 ) አል ረሕማን - Aya 63
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?› አል ረሕማን - Aya 63
مُدْهَامَّتَانِ ( 64 ) አል ረሕማን - Aya 64
ከልምላሜያቸው የተነሳ ወደ ጥቁረት ያዘነበሉ ናቸው፡፡ አል ረሕማን - Aya 64
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ( 65 ) አል ረሕማን - Aya 65
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ? አል ረሕማን - Aya 65
فِيهِمَا عَيْنَانِ نَضَّاخَتَانِ ( 66 ) አል ረሕማን - Aya 66
በውስጣቸው ሁለት የሚንፏፉ ምንጮች አልሉ፡፡ አል ረሕማን - Aya 66
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ( 67 ) አል ረሕማን - Aya 67
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ? አል ረሕማን - Aya 67
فِيهِمَا فَاكِهَةٌ وَنَخْلٌ وَرُمَّانٌ ( 68 ) አል ረሕማን - Aya 68
በውስጣቸው ፍራፍሬ፣ ዘምባባም፣ ሩማንም አልለ፡፡ አል ረሕማን - Aya 68
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ( 69 ) አል ረሕማን - Aya 69
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ? አል ረሕማን - Aya 69
فِيهِنَّ خَيْرَاتٌ حِسَانٌ ( 70 ) አል ረሕማን - Aya 70
በውስጣቸው ጠባየ መልካሞች መልክ ውቦች (ሴቶች) አልሉ፡፡ አል ረሕማን - Aya 70
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ( 71 ) አል ረሕማን - Aya 71
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ? አል ረሕማን - Aya 71
حُورٌ مَّقْصُورَاتٌ فِي الْخِيَامِ ( 72 ) አል ረሕማን - Aya 72
በድንኳኖች ውስጥ የተጨጎሉ የዓይኖቻቸው ጥቁረትና ንጣት ደማቅ የኾኑ ናቸው፡፡ አል ረሕማን - Aya 72
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ( 73 ) አል ረሕማን - Aya 73
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ? አል ረሕማን - Aya 73
لَمْ يَطْمِثْهُنَّ إِنسٌ قَبْلَهُمْ وَلَا جَانٌّ ( 74 ) አል ረሕማን - Aya 74
ከነርሱ በፊት ሰውም ጃንም አልገሰሳቸውም፡፡ አል ረሕማን - Aya 74
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ( 75 ) አል ረሕማን - Aya 75
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባበላላችሁ? አል ረሕማን - Aya 75
مُتَّكِئِينَ عَلَىٰ رَفْرَفٍ خُضْرٍ وَعَبْقَرِيٍّ حِسَانٍ ( 76 ) አል ረሕማን - Aya 76
በሚያረገርጉ አረንጓዴ ምንጣፎችና በሚያማምሩ ስጋጃዎች ላይ የተደላደሉ ሲኾኑ (ይቀመጣሉ)፡፡ አል ረሕማን - Aya 76
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ( 77 ) አል ረሕማን - Aya 77
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ? አል ረሕማን - Aya 77
تَبَارَكَ اسْمُ رَبِّكَ ذِي الْجَلَالِ وَالْإِكْرَامِ ( 78 ) አል ረሕማን - Aya 78
የግርማና የመክበር ባለቤት የኾነው ጌታህ ስም ተባረከ፡፡ አል ረሕማን - Aya 78
Facebook Twitter Google+ Pinterest Reddit StumbleUpon Linkedin Tumblr Google Bookmarks Email

Select Translation

Select surah