አማርኛ Muhammad Sadiq & Sani Habib
Surah አል ረሕማን - Aya count 78
الرَّحْمَٰنُ
( 1 ) 
አል-ረሕማን፤

عَلَّمَ الْقُرْآنَ
( 2 ) 
ቁርኣንን አስተማረ፡፡

خَلَقَ الْإِنسَانَ
( 3 ) 
ሰውን ፈጠረ፡፡

عَلَّمَهُ الْبَيَانَ
( 4 ) 
መናገርን አስተማረው፡፡

الشَّمْسُ وَالْقَمَرُ بِحُسْبَانٍ
( 5 ) 
ፀሐይና ጨረቃ በተወሰነ ልክ (ይኼዳሉ)፡፡

وَالنَّجْمُ وَالشَّجَرُ يَسْجُدَانِ
( 6 ) 
ሐረግና ዛፍም (ለእርሱ) ይሰግዳሉ፡፡

وَالسَّمَاءَ رَفَعَهَا وَوَضَعَ الْمِيزَانَ
( 7 ) 
ሰማይንም አጓናት፡፡ ትክክለኛነትንም ደነገገ፡፡

أَلَّا تَطْغَوْا فِي الْمِيزَانِ
( 8 ) 
በሚዛን (ስትመዝኑ) እንዳትበድሉ፡፡

وَأَقِيمُوا الْوَزْنَ بِالْقِسْطِ وَلَا تُخْسِرُوا الْمِيزَانَ
( 9 ) 
መመዘንንም በትክክል መዝኑ፡፡ ተመዛኙንም አታጉድሉ፡፡

وَالْأَرْضَ وَضَعَهَا لِلْأَنَامِ
( 10 ) 
ምድርንም ለፍጡሩ አደላደላት፡፡

فِيهَا فَاكِهَةٌ وَالنَّخْلُ ذَاتُ الْأَكْمَامِ
( 11 ) 
በውስጧ እሸት ባለ ሺፋኖች የኾኑ ዘንባባዎችም ያሉባት ስትኾን፡፡

وَالْحَبُّ ذُو الْعَصْفِ وَالرَّيْحَانُ
( 12 ) 
የገለባ ባለቤት የኾነ ቅንጣትም፡፡ ባለ መልካም መዐዛ ቅጠሎችም (ያሉባት ስትኾን)፡፡

فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
( 13 ) 
(ሰዎችና ጋኔኖች ሆይ!) ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

خَلَقَ الْإِنسَانَ مِن صَلْصَالٍ كَالْفَخَّارِ
( 14 ) 
ሰውን እንደ ሸክላ ከሚቅጨለጨል ደረቅ ጭቃ ፈጠረው፡፡

وَخَلَقَ الْجَانَّ مِن مَّارِجٍ مِّن نَّارٍ
( 15 ) 
ጃንንም ከእሳት ከኾነ ነበልባል ፈጠረው፡፡

فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
( 16 ) 
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

رَبُّ الْمَشْرِقَيْنِ وَرَبُّ الْمَغْرِبَيْنِ
( 17 ) 
የሁለቱ ምሥራቆች ጌታ፤ የሁለቱ ምዕራቦችም ጌታ ነው፡፡

فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
( 18 ) 
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

مَرَجَ الْبَحْرَيْنِ يَلْتَقِيَانِ
( 19 ) 
ሁለቱን ባሕሮች የሚገናኙ ሲኾኑ ለቀቃቸው፡፡

بَيْنَهُمَا بَرْزَخٌ لَّا يَبْغِيَانِ
( 20 ) 
(እንዳይዋሐዱ) በመካከላቸው ጋራጅ አልለ፡፡ (አንዱ ባንዱ ላይ) ወሰን አያልፉም፡፡

فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
( 21 ) 
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታሰተባብላላችሁ?›

يَخْرُجُ مِنْهُمَا اللُّؤْلُؤُ وَالْمَرْجَانُ
( 22 ) 
ሉልና መርጃን ከሁለቱ ይወጣል፡፡

فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
( 23 ) 
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

وَلَهُ الْجَوَارِ الْمُنشَآتُ فِي الْبَحْرِ كَالْأَعْلَامِ
( 24 ) 
እንደ ጋራዎች ኾነው በባሕር ውስጥ የተሠሩት ተንሻለዮቹም (ታንኳዎች) የእርሱ ናቸው፡፡

فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
( 25 ) 
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

كُلُّ مَنْ عَلَيْهَا فَانٍ
( 26 ) 
በእርሷ (በምድር) ላይ ያለው ሁሉ ጠፊ ነው፡፡

وَيَبْقَىٰ وَجْهُ رَبِّكَ ذُو الْجَلَالِ وَالْإِكْرَامِ
( 27 ) 
የልቅናና የልግሥና ባለቤት የኾነው የጌታህ ፊትም ይቀራል፡፡ (አይጠፋም)፡፡

فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
( 28 ) 
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

يَسْأَلُهُ مَن فِي السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ ۚ كُلَّ يَوْمٍ هُوَ فِي شَأْنٍ
( 29 ) 
በሰማያትና በምድር ውስጥ ያሉት ሁሉ ይለምኑታል፡፡ በየቀኑ ሁሉ እርሱ በሥራ ላይ ነው፡፡

فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
( 30 ) 
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታሰተባብላላችሁ?›

سَنَفْرُغُ لَكُمْ أَيُّهَ الثَّقَلَانِ
( 31 ) 
እናንተ ሁለት ከባዶች (ሰዎችና ጋኔኖች) ሆይ! ለእናንተ (መቆጣጠር) በእርግጥ እናስባለን፡፡

فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
( 32 ) 
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

يَا مَعْشَرَ الْجِنِّ وَالْإِنسِ إِنِ اسْتَطَعْتُمْ أَن تَنفُذُوا مِنْ أَقْطَارِ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ فَانفُذُوا ۚ لَا تَنفُذُونَ إِلَّا بِسُلْطَانٍ
( 33 ) 
የጋኔንና የሰው ጭፍሮች ሆይ! ከሰማያትና ከምድር ቀበሌዎች መውጣትን ብትችሉ ውጡ፡፡ በስልጣን እንጅ አትወጡም፡፡ (ግን ስልጣን የላችሁም)

فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
( 34 ) 
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

يُرْسَلُ عَلَيْكُمَا شُوَاظٌ مِّن نَّارٍ وَنُحَاسٌ فَلَا تَنتَصِرَانِ
( 35 ) 
በሁለታችሁም ላይ ከእሳት ነበልባል፣ ጭስም ይላክባችኋል፡፡ (ሁለታችሁም) አትርረዱምም፡፡

فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
( 36 ) 
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

فَإِذَا انشَقَّتِ السَّمَاءُ فَكَانَتْ وَرْدَةً كَالدِّهَانِ
( 37 ) 
ሰማይም በተሰነጠቀችና እንደ ጽጌረዳ፣ እንደታረበ ቆዳ በኾነች ጊዜ፤ (ጭንቁን ምን አበረታው)፡፡

فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
( 38 ) 
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

فَيَوْمَئِذٍ لَّا يُسْأَلُ عَن ذَنبِهِ إِنسٌ وَلَا جَانٌّ
( 39 ) 
በዚያም ቀን ሰውም ጃንም ከኃጢኣቱ ገና አይጠየቅም፡፡

فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
( 40 ) 
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

يُعْرَفُ الْمُجْرِمُونَ بِسِيمَاهُمْ فَيُؤْخَذُ بِالنَّوَاصِي وَالْأَقْدَامِ
( 41 ) 
ከሓዲዎች በምልክታቸው ይታወቃሉ፡፡ አናቶቻቸውንና ጫማዎቻቸውንም ይያዛሉ፡፡

فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
( 42 ) 
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ፡፡

هَٰذِهِ جَهَنَّمُ الَّتِي يُكَذِّبُ بِهَا الْمُجْرِمُونَ
( 43 ) 
ይህቺ ያቺ አመጸኞች በእርሷ ያስተባብሉባት የነበረችው ገሀነም ናት (ይባላሉ)፡፡

يَطُوفُونَ بَيْنَهَا وَبَيْنَ حَمِيمٍ آنٍ
( 44 ) 
በእርሷና በጣም ሞቃት በኾነ ፍል ውሃ መካከል ይመላለሳሉ፡፡

فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
( 45 ) 
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

وَلِمَنْ خَافَ مَقَامَ رَبِّهِ جَنَّتَانِ
( 46 ) 
በጌታውም ፊት መቆምን ለፈራ ሰው ሁለት ገነቶች አልሉት፡፡

فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
( 47 ) 
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

ذَوَاتَا أَفْنَانٍ
( 48 ) 
የቀንዘሎች ባለ ቤቶች የኾኑ (ገነቶች አልሉት)፡፡

فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
( 49 ) 
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

فِيهِمَا عَيْنَانِ تَجْرِيَانِ
( 50 ) 
በሁለቱ ውስጥ የሚፈስሱ ሁለት ምንጮች አልሉ፡፡

فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
( 51 ) 
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

فِيهِمَا مِن كُلِّ فَاكِهَةٍ زَوْجَانِ
( 52 ) 
በሁለቱ ውስጥ ከፍራፍሬዎች ሁሉ ሁለት ዓይነቶች (እርጥብና ደረቅ) አልሉ፡፡

فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
( 53 ) 
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

مُتَّكِئِينَ عَلَىٰ فُرُشٍ بَطَائِنُهَا مِنْ إِسْتَبْرَقٍ ۚ وَجَنَى الْجَنَّتَيْنِ دَانٍ
( 54 ) 
የውስጥ ጉስጉሳቸው ከወፍራም ሐር በኾኑ ምንጣፎች ላይ የተመቻቹ ሲኾኑ (ይንፈላሰሳሉ)፡፡ የሁለቱም ገነቶች ፍሬ (ለለቃሚ) ቅርብ ነው፡፡

فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
( 55 ) 
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

فِيهِنَّ قَاصِرَاتُ الطَّرْفِ لَمْ يَطْمِثْهُنَّ إِنسٌ قَبْلَهُمْ وَلَا جَانٌّ
( 56 ) 
በውስጣቸው ከበፊታቸው (ከባሎቻቸው በፊት) ሰውም ጃንም ያልገሰሳቸው ዓይኖቻቸውን (በባሎቻቸው ላይ) አሳጣሪዎች (ሴቶች) አልሉ፡፡

فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
( 57 ) 
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

كَأَنَّهُنَّ الْيَاقُوتُ وَالْمَرْجَانُ
( 58 ) 
ልክ ያቁትና መርጃን ይመስላሉ፡፡

فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
( 59 ) 
ከጌታችሁም ጸጋዎቸ በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

هَلْ جَزَاءُ الْإِحْسَانِ إِلَّا الْإِحْسَانُ
( 60 ) 
የበጎ ሥራ ዋጋ በጎ እንጅ ሌላ ነውን?

فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
( 61 ) 
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

وَمِن دُونِهِمَا جَنَّتَانِ
( 62 ) 
ከሁለቱ ገነቶችም ሌላ ሁለት ገነቶች አልሉ፡፡

فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
( 63 ) 
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?›

مُدْهَامَّتَانِ
( 64 ) 
ከልምላሜያቸው የተነሳ ወደ ጥቁረት ያዘነበሉ ናቸው፡፡

فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
( 65 ) 
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

فِيهِمَا عَيْنَانِ نَضَّاخَتَانِ
( 66 ) 
በውስጣቸው ሁለት የሚንፏፉ ምንጮች አልሉ፡፡

فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
( 67 ) 
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

فِيهِمَا فَاكِهَةٌ وَنَخْلٌ وَرُمَّانٌ
( 68 ) 
በውስጣቸው ፍራፍሬ፣ ዘምባባም፣ ሩማንም አልለ፡፡

فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
( 69 ) 
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

فِيهِنَّ خَيْرَاتٌ حِسَانٌ
( 70 ) 
በውስጣቸው ጠባየ መልካሞች መልክ ውቦች (ሴቶች) አልሉ፡፡

فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
( 71 ) 
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

حُورٌ مَّقْصُورَاتٌ فِي الْخِيَامِ
( 72 ) 
በድንኳኖች ውስጥ የተጨጎሉ የዓይኖቻቸው ጥቁረትና ንጣት ደማቅ የኾኑ ናቸው፡፡

فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
( 73 ) 
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

لَمْ يَطْمِثْهُنَّ إِنسٌ قَبْلَهُمْ وَلَا جَانٌّ
( 74 ) 
ከነርሱ በፊት ሰውም ጃንም አልገሰሳቸውም፡፡

فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
( 75 ) 
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባበላላችሁ?

مُتَّكِئِينَ عَلَىٰ رَفْرَفٍ خُضْرٍ وَعَبْقَرِيٍّ حِسَانٍ
( 76 ) 
በሚያረገርጉ አረንጓዴ ምንጣፎችና በሚያማምሩ ስጋጃዎች ላይ የተደላደሉ ሲኾኑ (ይቀመጣሉ)፡፡

فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
( 77 ) 
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

تَبَارَكَ اسْمُ رَبِّكَ ذِي الْجَلَالِ وَالْإِكْرَامِ
( 78 ) 
የግርማና የመክበር ባለቤት የኾነው ጌታህ ስም ተባረከ፡፡
