አማርኛ Muhammad Sadiq & Sani Habib
Surah አል ተክዊር - Aya count 29
إِذَا الشَّمْسُ كُوِّرَتْ
( 1 ) 
ፀሐይ በተጠቀለለች ጊዜ፤

وَإِذَا النُّجُومُ انكَدَرَتْ
( 2 ) 
ከዋክብትም በረገፉ ጊዜ፤

وَإِذَا الْجِبَالُ سُيِّرَتْ
( 3 ) 
ተራራዎችም በተነዱ ጊዜ፤

وَإِذَا الْعِشَارُ عُطِّلَتْ
( 4 ) 
የዐሥር ወር እርጉዞች ግመሎችም (ያለጠባቂ) በተተዉ ጊዜ፤

وَإِذَا الْوُحُوشُ حُشِرَتْ
( 5 ) 
እንስሳትም ሁሉ በተሰበሰቡ ጊዜ፤

وَإِذَا الْبِحَارُ سُجِّرَتْ
( 6 ) 
ባሕሮችም በተቃጠሉ ጊዜ፤

وَإِذَا النُّفُوسُ زُوِّجَتْ
( 7 ) 
ነፍሶችም (በየአካሎቻቸው) በተቆራኙ ጊዜ፤

وَإِذَا الْمَوْءُودَةُ سُئِلَتْ
( 8 ) 
በሕይወቷ የተቀበረችውም ሴት ልጅ በተጠየቀች ጊዜ፤

بِأَيِّ ذَنبٍ قُتِلَتْ
( 9 ) 
በምን ወንጀል እንደ ተገደለች፤

وَإِذَا الصُّحُفُ نُشِرَتْ
( 10 ) 
ጽሑፎችም በተዘረጉ ጊዜ፤

وَإِذَا السَّمَاءُ كُشِطَتْ
( 11 ) 
ሰማይም በተገሸለጠች ጊዜ፤

وَإِذَا الْجَحِيمُ سُعِّرَتْ
( 12 ) 
ገሀነምም በተነደደች ጊዜ፤

وَإِذَا الْجَنَّةُ أُزْلِفَتْ
( 13 ) 
ገነትም በተቀረበች ጊዜ፤

عَلِمَتْ نَفْسٌ مَّا أَحْضَرَتْ
( 14 ) 
ነፍስ ሁሉ (ከሥራ) ያቀረበችውን ታውቃለች፤

فَلَا أُقْسِمُ بِالْخُنَّسِ
( 15 ) 
ተመላሾችም በኾኑት (ዐዋድያት) እምላለሁ፡፡

الْجَوَارِ الْكُنَّسِ
( 16 ) 
ኺያጆች ገቢዎች በኾኑት (ከዋክብት)፡፡

وَاللَّيْلِ إِذَا عَسْعَسَ
( 17 ) 
በሌሊቱም (ጨለማውን) በጠነሰሰ ጊዜ፤

وَالصُّبْحِ إِذَا تَنَفَّسَ
( 18 ) 
በንጋቱም (በብርሃን) በተነፈሰ ጊዜ፤ (እምላለሁ)፡፡

إِنَّهُ لَقَوْلُ رَسُولٍ كَرِيمٍ
( 19 ) 
እርሱ (ቁርኣን) የክቡር መልክተኛ ቃል ነው፡፡

ذِي قُوَّةٍ عِندَ ذِي الْعَرْشِ مَكِينٍ
( 20 ) 
የኀይል ባለቤት በዙፋኑ ባለ ቤት ዘንድ ባለሟል የኾነ፡፡

مُّطَاعٍ ثَمَّ أَمِينٍ
( 21 ) 
በዚያ ስፍራ ትእዛዙ ተሰሚ፤ ታማኝ የኾነ (መልክተኛ ቃል) ነው፡፡

وَمَا صَاحِبُكُم بِمَجْنُونٍ
( 22 ) 
ነቢያችሁም በፍጹም ዕብድ አይደለም፡፡

وَلَقَدْ رَآهُ بِالْأُفُقِ الْمُبِينِ
( 23 ) 
በግልጹ አድማስም በእርግጥ አይቶታል፡፡

وَمَا هُوَ عَلَى الْغَيْبِ بِضَنِينٍ
( 24 ) 
እርሱም በሩቁ ወሬ ላይ ሰሳች (ንፉግ) አይደለም፡፡

وَمَا هُوَ بِقَوْلِ شَيْطَانٍ رَّجِيمٍ
( 25 ) 
እርሱም (ቁርኣን) የእርጉም ሰይጣን ቃል አይደለም፡፡

فَأَيْنَ تَذْهَبُونَ
( 26 ) 
ታዲያ ወዴት ትኼዳላችሁ?

إِنْ هُوَ إِلَّا ذِكْرٌ لِّلْعَالَمِينَ
( 27 ) 
እርሱ የዓለማት መገሠጫ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡

لِمَن شَاءَ مِنكُمْ أَن يَسْتَقِيمَ
( 28 ) 
ከናንተ ቀጥተኛ መኾንን ለሻ ሰው (መገሰጫ ነው)፡፡

وَمَا تَشَاءُونَ إِلَّا أَن يَشَاءَ اللَّهُ رَبُّ الْعَالَمِينَ
( 29 ) 
የዓለማት ጌታ አላህ ካልሻም አትሹም፡፡
