Surah አል ተክዊር

አማርኛ Muhammad Sadiq & Sani Habib

Surah አል ተክዊር - Aya count 29
Facebook Twitter Google+ Pinterest Reddit StumbleUpon Linkedin Tumblr Google Bookmarks Email
إِذَا الشَّمْسُ كُوِّرَتْ ( 1 ) አል ተክዊር - Aya 1
ፀሐይ በተጠቀለለች ጊዜ፤ አል ተክዊር - Aya 1
وَإِذَا النُّجُومُ انكَدَرَتْ ( 2 ) አል ተክዊር - Aya 2
ከዋክብትም በረገፉ ጊዜ፤ አል ተክዊር - Aya 2
وَإِذَا الْجِبَالُ سُيِّرَتْ ( 3 ) አል ተክዊር - Aya 3
ተራራዎችም በተነዱ ጊዜ፤ አል ተክዊር - Aya 3
وَإِذَا الْعِشَارُ عُطِّلَتْ ( 4 ) አል ተክዊር - Aya 4
የዐሥር ወር እርጉዞች ግመሎችም (ያለጠባቂ) በተተዉ ጊዜ፤ አል ተክዊር - Aya 4
وَإِذَا الْوُحُوشُ حُشِرَتْ ( 5 ) አል ተክዊር - Aya 5
እንስሳትም ሁሉ በተሰበሰቡ ጊዜ፤ አል ተክዊር - Aya 5
وَإِذَا الْبِحَارُ سُجِّرَتْ ( 6 ) አል ተክዊር - Aya 6
ባሕሮችም በተቃጠሉ ጊዜ፤ አል ተክዊር - Aya 6
وَإِذَا النُّفُوسُ زُوِّجَتْ ( 7 ) አል ተክዊር - Aya 7
ነፍሶችም (በየአካሎቻቸው) በተቆራኙ ጊዜ፤ አል ተክዊር - Aya 7
وَإِذَا الْمَوْءُودَةُ سُئِلَتْ ( 8 ) አል ተክዊር - Aya 8
በሕይወቷ የተቀበረችውም ሴት ልጅ በተጠየቀች ጊዜ፤ አል ተክዊር - Aya 8
بِأَيِّ ذَنبٍ قُتِلَتْ ( 9 ) አል ተክዊር - Aya 9
በምን ወንጀል እንደ ተገደለች፤ አል ተክዊር - Aya 9
وَإِذَا الصُّحُفُ نُشِرَتْ ( 10 ) አል ተክዊር - Aya 10
ጽሑፎችም በተዘረጉ ጊዜ፤ አል ተክዊር - Aya 10
وَإِذَا السَّمَاءُ كُشِطَتْ ( 11 ) አል ተክዊር - Aya 11
ሰማይም በተገሸለጠች ጊዜ፤ አል ተክዊር - Aya 11
وَإِذَا الْجَحِيمُ سُعِّرَتْ ( 12 ) አል ተክዊር - Aya 12
ገሀነምም በተነደደች ጊዜ፤ አል ተክዊር - Aya 12
وَإِذَا الْجَنَّةُ أُزْلِفَتْ ( 13 ) አል ተክዊር - Aya 13
ገነትም በተቀረበች ጊዜ፤ አል ተክዊር - Aya 13
عَلِمَتْ نَفْسٌ مَّا أَحْضَرَتْ ( 14 ) አል ተክዊር - Aya 14
ነፍስ ሁሉ (ከሥራ) ያቀረበችውን ታውቃለች፤ አል ተክዊር - Aya 14
فَلَا أُقْسِمُ بِالْخُنَّسِ ( 15 ) አል ተክዊር - Aya 15
ተመላሾችም በኾኑት (ዐዋድያት) እምላለሁ፡፡ አል ተክዊር - Aya 15
الْجَوَارِ الْكُنَّسِ ( 16 ) አል ተክዊር - Aya 16
ኺያጆች ገቢዎች በኾኑት (ከዋክብት)፡፡ አል ተክዊር - Aya 16
وَاللَّيْلِ إِذَا عَسْعَسَ ( 17 ) አል ተክዊር - Aya 17
በሌሊቱም (ጨለማውን) በጠነሰሰ ጊዜ፤ አል ተክዊር - Aya 17
وَالصُّبْحِ إِذَا تَنَفَّسَ ( 18 ) አል ተክዊር - Aya 18
በንጋቱም (በብርሃን) በተነፈሰ ጊዜ፤ (እምላለሁ)፡፡ አል ተክዊር - Aya 18
إِنَّهُ لَقَوْلُ رَسُولٍ كَرِيمٍ ( 19 ) አል ተክዊር - Aya 19
እርሱ (ቁርኣን) የክቡር መልክተኛ ቃል ነው፡፡ አል ተክዊር - Aya 19
ذِي قُوَّةٍ عِندَ ذِي الْعَرْشِ مَكِينٍ ( 20 ) አል ተክዊር - Aya 20
የኀይል ባለቤት በዙፋኑ ባለ ቤት ዘንድ ባለሟል የኾነ፡፡ አል ተክዊር - Aya 20
مُّطَاعٍ ثَمَّ أَمِينٍ ( 21 ) አል ተክዊር - Aya 21
በዚያ ስፍራ ትእዛዙ ተሰሚ፤ ታማኝ የኾነ (መልክተኛ ቃል) ነው፡፡ አል ተክዊር - Aya 21
وَمَا صَاحِبُكُم بِمَجْنُونٍ ( 22 ) አል ተክዊር - Aya 22
ነቢያችሁም በፍጹም ዕብድ አይደለም፡፡ አል ተክዊር - Aya 22
وَلَقَدْ رَآهُ بِالْأُفُقِ الْمُبِينِ ( 23 ) አል ተክዊር - Aya 23
በግልጹ አድማስም በእርግጥ አይቶታል፡፡ አል ተክዊር - Aya 23
وَمَا هُوَ عَلَى الْغَيْبِ بِضَنِينٍ ( 24 ) አል ተክዊር - Aya 24
እርሱም በሩቁ ወሬ ላይ ሰሳች (ንፉግ) አይደለም፡፡ አል ተክዊር - Aya 24
وَمَا هُوَ بِقَوْلِ شَيْطَانٍ رَّجِيمٍ ( 25 ) አል ተክዊር - Aya 25
እርሱም (ቁርኣን) የእርጉም ሰይጣን ቃል አይደለም፡፡ አል ተክዊር - Aya 25
فَأَيْنَ تَذْهَبُونَ ( 26 ) አል ተክዊር - Aya 26
ታዲያ ወዴት ትኼዳላችሁ? አል ተክዊር - Aya 26
إِنْ هُوَ إِلَّا ذِكْرٌ لِّلْعَالَمِينَ ( 27 ) አል ተክዊር - Aya 27
እርሱ የዓለማት መገሠጫ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡ አል ተክዊር - Aya 27
لِمَن شَاءَ مِنكُمْ أَن يَسْتَقِيمَ ( 28 ) አል ተክዊር - Aya 28
ከናንተ ቀጥተኛ መኾንን ለሻ ሰው (መገሰጫ ነው)፡፡ አል ተክዊር - Aya 28
وَمَا تَشَاءُونَ إِلَّا أَن يَشَاءَ اللَّهُ رَبُّ الْعَالَمِينَ ( 29 ) አል ተክዊር - Aya 29
የዓለማት ጌታ አላህ ካልሻም አትሹም፡፡ አል ተክዊር - Aya 29
Facebook Twitter Google+ Pinterest Reddit StumbleUpon Linkedin Tumblr Google Bookmarks Email

Select Translation

Select surah