አማርኛ Muhammad Sadiq & Sani Habib
Surah አል ዋቂዓህ - Aya count 96
إِذَا وَقَعَتِ الْوَاقِعَةُ
( 1 ) 
መከራይቱ በወደቀች ጊዜ፡፡

لَيْسَ لِوَقْعَتِهَا كَاذِبَةٌ
( 2 ) 
ለመውደቋ አስተባባይ (ነፍስ) የለችም፡፡

خَافِضَةٌ رَّافِعَةٌ
( 3 ) 
ዝቅ አድራጊና ከፍ አድራጊ ናት፡፡

إِذَا رُجَّتِ الْأَرْضُ رَجًّا
( 4 ) 
ምድር መናወጥን በተናወጠች ጊዜ፡፡

وَبُسَّتِ الْجِبَالُ بَسًّا
( 5 ) 
ተራራዎችም መፍፈርፈርን በተፈረፈሩ ጊዜ (እንደተፈጨ ዱቄት በኾኑ ጊዜ)፡፡

فَكَانَتْ هَبَاءً مُّنبَثًّا
( 6 ) 
የተበተነ ብናኝ በኾኑም ጊዜ

وَكُنتُمْ أَزْوَاجًا ثَلَاثَةً
( 7 ) 
ሦስት ዓይነቶችም በኾናችሁ ጊዜ (ታዋርዳለች፤ ታነሳለችም)፡፡

فَأَصْحَابُ الْمَيْمَنَةِ مَا أَصْحَابُ الْمَيْمَنَةِ
( 8 ) 
የቀኝ ጓዶችም ምን (የተከበሩ) የቀኝ ጓዶች ናቸው፡፡

وَأَصْحَابُ الْمَشْأَمَةِ مَا أَصْحَابُ الْمَشْأَمَةِ
( 9 ) 
የግራ ጓዶችም ምን (የተዋረዱ) የግራ ጓዶች ናቸው፡፡

وَالسَّابِقُونَ السَّابِقُونَ
( 10 ) 
(ለበጎ ሥራ) ቀዳሚዎቹም (ለገነት) ቀዳሚዎች ናቸው፡፡

أُولَٰئِكَ الْمُقَرَّبُونَ
( 11 ) 
እነዚያ ባለሟሎቹ ናቸው፡፡

فِي جَنَّاتِ النَّعِيمِ
( 12 ) 
በመጠቀሚያ ገነቶች ውስጥ ሲኾኑ፡፡

ثُلَّةٌ مِّنَ الْأَوَّلِينَ
( 13 ) 
ከፊተኞቹ ብዙ ጭፍሮች ናቸው፡፡

وَقَلِيلٌ مِّنَ الْآخِرِينَ
( 14 ) 
ከኋለኞቹም ጥቂቶች ናቸው፡፡

عَلَىٰ سُرُرٍ مَّوْضُونَةٍ
( 15 ) 
በተታቱ አልጋዎች ላይ ይኾናሉ፡፡

مُّتَّكِئِينَ عَلَيْهَا مُتَقَابِلِينَ
( 16 ) 
በእርሷ ላይ የተመቻቹና ፊት ለፊት የተቅጣጩ ሲኾኑ፡፡

يَطُوفُ عَلَيْهِمْ وِلْدَانٌ مُّخَلَّدُونَ
( 17 ) 
በእነርሱ ላይ ሁል ጊዜ የማያረጁ ወጣቶች ልጆች ይዘዋወራሉ፡፡

بِأَكْوَابٍ وَأَبَارِيقَ وَكَأْسٍ مِّن مَّعِينٍ
( 18 ) 
ከጠጅ ምንጭም በብርጭቆዎችና በኩስኩስቶች በጽዋም (በእነርሱ ላይ ይዝዞራሉ)፡፡

لَّا يُصَدَّعُونَ عَنْهَا وَلَا يُنزِفُونَ
( 19 ) 
ከእርሷ የራስ ምታት አያገኛቸውም፤ አይሰክሩምም፡፡

وَفَاكِهَةٍ مِّمَّا يَتَخَيَّرُونَ
( 20 ) 
ከሚመርጡትም ዓይነት በእሸቶች፡፡

وَلَحْمِ طَيْرٍ مِّمَّا يَشْتَهُونَ
( 21 ) 
ከሚሹትም በኾነ የበራሪ ሥጋ (ይዞሩባቸዋል)፡፡

وَحُورٌ عِينٌ
( 22 ) 
ዓይናማዎች የኾኑ ነጫጭ ቆንጆዎችም አሏቸው፡፡

كَأَمْثَالِ اللُّؤْلُؤِ الْمَكْنُونِ
( 23 ) 
ልክ እንደተሸፈነ ሉል መሰሎች የኾኑ፡፡

جَزَاءً بِمَا كَانُوا يَعْمَلُونَ
( 24 ) 
በዚያ ይሠሩት በነበሩት ምክንያት ዋጋ ይኾን ዘንድ (ይህንን አደረግንላቸው)፡፡

لَا يَسْمَعُونَ فِيهَا لَغْوًا وَلَا تَأْثِيمًا
( 25 ) 
በውስጥዋ ውድቅ ንግግርንና መውወንጀልን አይሰሙም፡፡

إِلَّا قِيلًا سَلَامًا سَلَامًا
( 26 ) 
ግን ሰላም መባባልን (ይሰማሉ)፡፡

وَأَصْحَابُ الْيَمِينِ مَا أَصْحَابُ الْيَمِينِ
( 27 ) 
የቀኝም ጓዶች ምንኛ (የከበሩ) የቀኝ ጓዶች!

فِي سِدْرٍ مَّخْضُودٍ
( 28 ) 
በተቀፈቀፈ (እሾህ በሌለው) ቁርቁራ ውስጥ ናቸው፡፡

وَطَلْحٍ مَّنضُودٍ
( 29 ) 
(ፍሬው) በተነባበረ በሙዝ ዛፍም፡፡

وَظِلٍّ مَّمْدُودٍ
( 30 ) 
በተዘረጋ ጥላ ሥርም፡፡

وَمَاءٍ مَّسْكُوبٍ
( 31 ) 
በሚንቧቧ ውሃ አጠገብም፡፡

وَفَاكِهَةٍ كَثِيرَةٍ
( 32 ) 
ብዙ (ዓይነት) በኾኑ ፍራፍሬዎችም፡፡

لَّا مَقْطُوعَةٍ وَلَا مَمْنُوعَةٍ
( 33 ) 
የማትቋረጥም የማትከለከልም የኾነች፡፡

وَفُرُشٍ مَّرْفُوعَةٍ
( 34 ) 
ከፍ በተደረጉ ምንጣፎችም (ሴቶችም መካከል)፡፡

إِنَّا أَنشَأْنَاهُنَّ إِنشَاءً
( 35 ) 
እኛ አዲስ ፍጥረት አድርገን (ለእነርሱ) ፈጠርናቸው፡፡

فَجَعَلْنَاهُنَّ أَبْكَارًا
( 36 ) 
ደናግሎችም አደረግናቸው፡፡

عُرُبًا أَتْرَابًا
( 37 ) 
ለባሎቻቸው ተሽሞርሟሪዎች እኩያዎች (አደረግናቸው)፡፡

لِّأَصْحَابِ الْيَمِينِ
( 38 ) 
ለቀኝ ጓዶች (አዘጋጀናቸው)፡፡

ثُلَّةٌ مِّنَ الْأَوَّلِينَ
( 39 ) 
ከፊተኞቹ ብዙ ጭፍሮች ናቸው፡፡

وَثُلَّةٌ مِّنَ الْآخِرِينَ
( 40 ) 
ከኋለኞቹም ብዙ ጭፍሮች ናቸው፡፡

وَأَصْحَابُ الشِّمَالِ مَا أَصْحَابُ الشِّمَالِ
( 41 ) 
የግራ ጓደኞችም ምንኛ (የተዋረዱ) የግራ ጓዶች! ናቸው፡፡

فِي سَمُومٍ وَحَمِيمٍ
( 42 ) 
በመርዛም ነፋስ በጣም በፈላ ውሃም ውስጥ ናቸው፡፡

وَظِلٍّ مِّن يَحْمُومٍ
( 43 ) 
ከጥቁር ጭስም በኾነ ጥላ ውስጥ፡፡

لَّا بَارِدٍ وَلَا كَرِيمٍ
( 44 ) 
ቀዝቃዛም መልካምም ያልኾነ፡፡

إِنَّهُمْ كَانُوا قَبْلَ ذَٰلِكَ مُتْرَفِينَ
( 45 ) 
እነርሱ ከዚህ በፊት ቅምጥሎች ነበሩና፡፡

وَكَانُوا يُصِرُّونَ عَلَى الْحِنثِ الْعَظِيمِ
( 46 ) 
በታላቅ ኀጢአትም ላይ ይዘወትሩ ነበሩና፡፡

وَكَانُوا يَقُولُونَ أَئِذَا مِتْنَا وَكُنَّا تُرَابًا وَعِظَامًا أَإِنَّا لَمَبْعُوثُونَ
( 47 ) 
ይሉም ነበሩ፡- «በሞትንና ዐፈር፣ ዐጥንቶችም በኾን ጊዜ እኛ በእርግጥ የምንቀሰቀስ ነን?

أَوَآبَاؤُنَا الْأَوَّلُونَ
( 48 ) 
«የፊተኞቹ አባቶቻችንም?»

قُلْ إِنَّ الْأَوَّلِينَ وَالْآخِرِينَ
( 49 ) 
በላቸው፡- «ፊተኞቹም ኋለኞቹም፡፡

لَمَجْمُوعُونَ إِلَىٰ مِيقَاتِ يَوْمٍ مَّعْلُومٍ
( 50 ) 
«በተወሰነ ቀን ቀጠሮ በእርግጥ ተሰብሳቢዎች ናቸው፡፡

ثُمَّ إِنَّكُمْ أَيُّهَا الضَّالُّونَ الْمُكَذِّبُونَ
( 51 ) 
«ከዚያም እናንተ ጠማሞች አስተባባዮች ሆይ!

لَآكِلُونَ مِن شَجَرٍ مِّن زَقُّومٍ
( 52 ) 
« ከዘቁም ዛፍ በእርግጥ በይዎች ናችሁ፡፡

فَمَالِئُونَ مِنْهَا الْبُطُونَ
( 53 ) 
«ከእርሷም ሆዶቻችሁን ሞይዎች ናችሁ፡፡

فَشَارِبُونَ عَلَيْهِ مِنَ الْحَمِيمِ
( 54 ) 
«በእርሱ ላይም ከፈላ ውሃ ጠጪዎች ናችሁ፡፡

فَشَارِبُونَ شُرْبَ الْهِيمِ
( 55 ) 
«የተጠሙንም ግመሎች አጠጣጥ ብጤ ጠጪዎች ናችሁ፡፡»

هَٰذَا نُزُلُهُمْ يَوْمَ الدِّينِ
( 56 ) 
ይህ በፍርዱ ቀን መስተንግዷቸው ነው፡፡

نَحْنُ خَلَقْنَاكُمْ فَلَوْلَا تُصَدِّقُونَ
( 57 ) 
እኛ ፈጠርናችሁ አታምኑምን?

أَفَرَأَيْتُم مَّا تُمْنُونَ
( 58 ) 
(በማኅፀኖች) የምታፈሱትን አያችሁን?

أَأَنتُمْ تَخْلُقُونَهُ أَمْ نَحْنُ الْخَالِقُونَ
( 59 ) 
እናንተ ትፈጥሩታላችሁን? ወይስ እኛ ፈጣሪዎቹን ነን?

نَحْنُ قَدَّرْنَا بَيْنَكُمُ الْمَوْتَ وَمَا نَحْنُ بِمَسْبُوقِينَ
( 60 ) 
እኛ ሞትን (ጊዜውን) በመካከላችሁ ወሰንን፡፡ እኛም ተሸናፊዎች አይደለንም፡፡

عَلَىٰ أَن نُّبَدِّلَ أَمْثَالَكُمْ وَنُنشِئَكُمْ فِي مَا لَا تَعْلَمُونَ
( 61 ) 
ብጤዎቻችሁን በመለወጥና በዚያ በማታውቁትም (ቅርጽ) እናንተን በመፍጠር ላይ (አንሸነፍም)፡፡

وَلَقَدْ عَلِمْتُمُ النَّشْأَةَ الْأُولَىٰ فَلَوْلَا تَذَكَّرُونَ
( 62 ) 
የፊተኛይቱንም አፈጣጠር በእርግጥ ዐውቃችኋል፡፡ አትገነዘቡምን?

أَفَرَأَيْتُم مَّا تَحْرُثُونَ
( 63 ) 
የምትዘሩትንም አያችሁን?

أَأَنتُمْ تَزْرَعُونَهُ أَمْ نَحْنُ الزَّارِعُونَ
( 64 ) 
እናንተ ታበቅሉታላችሁን? ወይስ እኛ አብቃዮቹ ነን?

لَوْ نَشَاءُ لَجَعَلْنَاهُ حُطَامًا فَظَلْتُمْ تَفَكَّهُونَ
( 65 ) 
ብነሻ ኖሮ ደረቅ ስብርብር ባደረግነውና የምትደነቁም በኾናችሁ ነበር፡፡

إِنَّا لَمُغْرَمُونَ
( 66 ) 
«እኛ በዕዳ ተያዦች ነን፡፡

بَلْ نَحْنُ مَحْرُومُونَ
( 67 ) 
«በእርግጥም እኛ (ከመጠቀም) የተከለከልን ነን» (ትሉ ነበር)፡፡

أَفَرَأَيْتُمُ الْمَاءَ الَّذِي تَشْرَبُونَ
( 68 ) 
ያንንም የምትጠጡትን ውሃ አየችሁን?

أَأَنتُمْ أَنزَلْتُمُوهُ مِنَ الْمُزْنِ أَمْ نَحْنُ الْمُنزِلُونَ
( 69 ) 
እናንተ ከደመናው አወረዳችሁትን? ወይስ እኛ አውራጆቹ ነን?

لَوْ نَشَاءُ جَعَلْنَاهُ أُجَاجًا فَلَوْلَا تَشْكُرُونَ
( 70 ) 
ብንሻ ኖሮ መርጋጋ ባደረግነው ነበር፡፡ አታመሰግኑምን?

أَفَرَأَيْتُمُ النَّارَ الَّتِي تُورُونَ
( 71 ) 
ያቺንም የምትሰብቋትን እሳት አያችሁን?

أَأَنتُمْ أَنشَأْتُمْ شَجَرَتَهَا أَمْ نَحْنُ الْمُنشِئُونَ
( 72 ) 
እናንተ ዛፏን ፈጠራችሁን? ወይስ እኛ ፈጣሪዎችዋ ነን?

نَحْنُ جَعَلْنَاهَا تَذْكِرَةً وَمَتَاعًا لِّلْمُقْوِينَ
( 73 ) 
እኛ (ለገሀናም) ማስታወሻ ለመንገደኞችም መጠቀሚያ አደረግናት፡፡

فَسَبِّحْ بِاسْمِ رَبِّكَ الْعَظِيمِ
( 74 ) 
የታላቁን ጌታህንም ስም አወድስ፡፡

فَلَا أُقْسِمُ بِمَوَاقِعِ النُّجُومِ
( 75 ) 
በከዋክብትም መጥለቂያዎች እምላለሁ፡፡

وَإِنَّهُ لَقَسَمٌ لَّوْ تَعْلَمُونَ عَظِيمٌ
( 76 ) 
እርሱም ብታወቁ ታላቅ መሓላ ነው፡፡

إِنَّهُ لَقُرْآنٌ كَرِيمٌ
( 77 ) 
እርሱ የከበረ ቁርኣን ነው፡፡

فِي كِتَابٍ مَّكْنُونٍ
( 78 ) 
በተጠበቀ መጽሐፍ ውስጥ ነው፡፡

لَّا يَمَسُّهُ إِلَّا الْمُطَهَّرُونَ
( 79 ) 
የተጥራሩት እንጅ ሌላ አይነካውም፡፡

تَنزِيلٌ مِّن رَّبِّ الْعَالَمِينَ
( 80 ) 
ከዓለማት ጌታ የተወረደ ነው፡፡

أَفَبِهَٰذَا الْحَدِيثِ أَنتُم مُّدْهِنُونَ
( 81 ) 
በዚህ ንግግር እናንተ ቸልተኞች ናችሁን?

وَتَجْعَلُونَ رِزْقَكُمْ أَنَّكُمْ تُكَذِّبُونَ
( 82 ) 
ሲሳያችሁንም (ዝናምን) እናንተ የምታስተባብሉት ታደርጋላችሁን?

فَلَوْلَا إِذَا بَلَغَتِ الْحُلْقُومَ
( 83 ) 
(ነፍስ) ጉረሮንም በደረሰች ጊዜ፡፡

وَأَنتُمْ حِينَئِذٍ تَنظُرُونَ
( 84 ) 
እናንተ ያን ጊዜ የምታዩ ስትኾኑ፡፡

وَنَحْنُ أَقْرَبُ إِلَيْهِ مِنكُمْ وَلَٰكِن لَّا تُبْصِرُونَ
( 85 ) 
እኛም ግን አታዩም እንጅ ከእናንተ ይልቅ ወደእርሱ የቀረብን ስንኾን፡፡

فَلَوْلَا إِن كُنتُمْ غَيْرَ مَدِينِينَ
( 86 ) 
የማትዳኙም ከኾናችሁ፡፡

تَرْجِعُونَهَا إِن كُنتُمْ صَادِقِينَ
( 87 ) 
እውነተኞች እንደ ኾናችሁ (ነፍሲቱን ወደ አካሉ) ለምን አትመልሷትም፡፡

فَأَمَّا إِن كَانَ مِنَ الْمُقَرَّبِينَ
( 88 ) 
(ሟቹ) ከባለሟሎቹ ቢኾንማ፡፡

فَرَوْحٌ وَرَيْحَانٌ وَجَنَّتُ نَعِيمٍ
( 89 ) 
(ለእርሱ) ዕረፍት፣ መልካም ሲሳይም፣ የመጠቀሚያ ገነትም አልለው፡፡

وَأَمَّا إِن كَانَ مِنْ أَصْحَابِ الْيَمِينِ
( 90 ) 
ከቀኝ ጓዶችም ቢኾንማ፡፡

فَسَلَامٌ لَّكَ مِنْ أَصْحَابِ الْيَمِينِ
( 91 ) 
ከቀኝ ጓዶች ስለ ኾንክ ላንተ ሰላም አልለህ (ይባላል)፡፡

وَأَمَّا إِن كَانَ مِنَ الْمُكَذِّبِينَ الضَّالِّينَ
( 92 ) 
ከሚያስዋሹት ጠማማዎችም ቢኾንማ፡፡

فَنُزُلٌ مِّنْ حَمِيمٍ
( 93 ) 
ከፈላ ውሃ የኾነ መስተንግዶ አልለው፡፡

وَتَصْلِيَةُ جَحِيمٍ
( 94 ) 
በገሀነም መቃጠልም (አልለው)፡፡

إِنَّ هَٰذَا لَهُوَ حَقُّ الْيَقِينِ
( 95 ) 
ይህ እርሱ እርግጠኛ እውነት ነው፡፡

فَسَبِّحْ بِاسْمِ رَبِّكَ الْعَظِيمِ
( 96 ) 
የታላቁንም ጌታህን ስም አወድስ፡፡
