Surah አል ዛሪያት

አማርኛ Muhammad Sadiq & Sani Habib

Surah አል ዛሪያት - Aya count 60
Facebook Twitter Google+ Pinterest Reddit StumbleUpon Linkedin Tumblr Google Bookmarks Email
وَالذَّارِيَاتِ ذَرْوًا ( 1 ) አል ዛሪያት - Aya 1
መበተንን በታኞች በኾኑት (ነፋሶች)፡፡ አል ዛሪያት - Aya 1
فَالْحَامِلَاتِ وِقْرًا ( 2 ) አል ዛሪያት - Aya 2
ከባድ (ዝናምን) ተሸካሚዎች በኾኑትም (ደመናዎች)፡፡ አል ዛሪያት - Aya 2
فَالْجَارِيَاتِ يُسْرًا ( 3 ) አል ዛሪያት - Aya 3
ገር (መንሻለልን) ተንሻላዮች በኾኑትም (መርከቦች)፡፡ አል ዛሪያት - Aya 3
فَالْمُقَسِّمَاتِ أَمْرًا ( 4 ) አል ዛሪያት - Aya 4
ነገርን ሁሉ አከፋፋዮች በኾኑትም (መላእክት) እምላለሁ፡፡ አል ዛሪያት - Aya 4
إِنَّمَا تُوعَدُونَ لَصَادِقٌ ( 5 ) አል ዛሪያት - Aya 5
የምትቀጠሩት (ትንሣኤ) እውነት ነው፡፡ አል ዛሪያት - Aya 5
وَإِنَّ الدِّينَ لَوَاقِعٌ ( 6 ) አል ዛሪያት - Aya 6
(እንደየሥራው) ዋጋን ማግኘትም፤ ኋኝ ነው፤ (የማይቀር ነው)፡፡ አል ዛሪያት - Aya 6
وَالسَّمَاءِ ذَاتِ الْحُبُكِ ( 7 ) አል ዛሪያት - Aya 7
የ(ከዋክብት) መንገዶች ባለቤት በኾነችው ሰማይ እምላለሁ፡፡ አል ዛሪያት - Aya 7
إِنَّكُمْ لَفِي قَوْلٍ مُّخْتَلِفٍ ( 8 ) አል ዛሪያት - Aya 8
እናንተ (የመካ ሰዎች) በተለያየ ቃል ውስጥ ናችሁ፡፡ አል ዛሪያት - Aya 8
يُؤْفَكُ عَنْهُ مَنْ أُفِكَ ( 9 ) አል ዛሪያት - Aya 9
ከርሱ የሚዝዞር ሰው ይዝዞራል፡፡ አል ዛሪያት - Aya 9
قُتِلَ الْخَرَّاصُونَ ( 10 ) አል ዛሪያት - Aya 10
በግምት የሚናገሩ ውሸታሞች ተረገሙ፡፡ አል ዛሪያት - Aya 10
الَّذِينَ هُمْ فِي غَمْرَةٍ سَاهُونَ ( 11 ) አል ዛሪያት - Aya 11
እነዚያ እነርሱ በሚሸፍን ስሕተተ ውስጥ ዘንጊዎች የኾኑት፡፡ አል ዛሪያት - Aya 11
يَسْأَلُونَ أَيَّانَ يَوْمُ الدِّينِ ( 12 ) አል ዛሪያት - Aya 12
የዋጋ መስጫው ቀን መቼ እንደ ኾነ ይጠይቃሉ፡፡ አል ዛሪያት - Aya 12
يَوْمَ هُمْ عَلَى النَّارِ يُفْتَنُونَ ( 13 ) አል ዛሪያት - Aya 13
(እነርሱ) በእሳት ላይ በሚፈተኑበት ቀን ነው፡፡ አል ዛሪያት - Aya 13
ذُوقُوا فِتْنَتَكُمْ هَٰذَا الَّذِي كُنتُم بِهِ تَسْتَعْجِلُونَ ( 14 ) አል ዛሪያት - Aya 14
«መከራችሁን ቅመሱ፤ ይህ ያ በእርሱ ትቻኮሉበት የነበራችሁት ነው» (ይባላሉ)፡፡ አል ዛሪያት - Aya 14
إِنَّ الْمُتَّقِينَ فِي جَنَّاتٍ وَعُيُونٍ ( 15 ) አል ዛሪያት - Aya 15
አላህን ፈሪዎቹ በአትክልቶችና በምንጮች ውስጥ ናቸው፡፡ አል ዛሪያት - Aya 15
آخِذِينَ مَا آتَاهُمْ رَبُّهُمْ ۚ إِنَّهُمْ كَانُوا قَبْلَ ذَٰلِكَ مُحْسِنِينَ ( 16 ) አል ዛሪያት - Aya 16
ያንን ጌታቸው የሰጣቸውን ተቀባዮች ኾነው፤ (በገነት ውስጥ ይኾናሉ)፡፡ እነርሱ ከዚህ በፊት መልካም ሰሪዎች ነበሩና፡፡ አል ዛሪያት - Aya 16
كَانُوا قَلِيلًا مِّنَ اللَّيْلِ مَا يَهْجَعُونَ ( 17 ) አል ዛሪያት - Aya 17
ከሌሊቱ ጥቂትን ብቻ ይተኙ ነበሩ፡፡ አል ዛሪያት - Aya 17
وَبِالْأَسْحَارِ هُمْ يَسْتَغْفِرُونَ ( 18 ) አል ዛሪያት - Aya 18
በሌሊቱ መጨረሻዎችም እነርሱ ምሕረትን ይለምናሉ፡፡ አል ዛሪያት - Aya 18
وَفِي أَمْوَالِهِمْ حَقٌّ لِّلسَّائِلِ وَالْمَحْرُومِ ( 19 ) አል ዛሪያት - Aya 19
በገንዘቦቻቸውም ውስጥ ለለማኝና (ከልመና) ለተከለከለም (በችሮታቸው) መብት አልለ፡፡ አል ዛሪያት - Aya 19
وَفِي الْأَرْضِ آيَاتٌ لِّلْمُوقِنِينَ ( 20 ) አል ዛሪያት - Aya 20
በምድርም ውስጥ ለሚያረጋግጡ ሰዎች ምልክቶች አልሉ፡፡ አል ዛሪያት - Aya 20
وَفِي أَنفُسِكُمْ ۚ أَفَلَا تُبْصِرُونَ ( 21 ) አል ዛሪያት - Aya 21
በነፍሶቻችሁም ውስጥ (ምልክቶች አልሉ)፤ ታዲያ አትመለከቱምን?› አል ዛሪያት - Aya 21
وَفِي السَّمَاءِ رِزْقُكُمْ وَمَا تُوعَدُونَ ( 22 ) አል ዛሪያት - Aya 22
ሲሳያችሁም የምትቀጠሩትም (ፍዳና ምንዳ) በሰማይ ውስጥ ነው፡፡ አል ዛሪያት - Aya 22
فَوَرَبِّ السَّمَاءِ وَالْأَرْضِ إِنَّهُ لَحَقٌّ مِّثْلَ مَا أَنَّكُمْ تَنطِقُونَ ( 23 ) አል ዛሪያት - Aya 23
በሰማይና በምድር ጌታም እምላለሁ፡፡ እርሱ እናንተ እንደምትናገሩት ብጤ እርግጠኛ ነው፡፡ አል ዛሪያት - Aya 23
هَلْ أَتَاكَ حَدِيثُ ضَيْفِ إِبْرَاهِيمَ الْمُكْرَمِينَ ( 24 ) አል ዛሪያት - Aya 24
የተከበሩት የኢብራሂም እንግዶች ወሬ መጥቶሃልን? አል ዛሪያት - Aya 24
إِذْ دَخَلُوا عَلَيْهِ فَقَالُوا سَلَامًا ۖ قَالَ سَلَامٌ قَوْمٌ مُّنكَرُونَ ( 25 ) አል ዛሪያት - Aya 25
በእርሱ ላይ በገቡና «ሰለም» ባሉ ጊዜ (አስታውስ)፡፡ «ሰላም ያልታወቃችሁ ሕዝቦች ናችሁ፤» አላቸው፡፡ አል ዛሪያት - Aya 25
فَرَاغَ إِلَىٰ أَهْلِهِ فَجَاءَ بِعِجْلٍ سَمِينٍ ( 26 ) አል ዛሪያት - Aya 26
ወደ ቤተሰቡም ተዘነበለ፤» ወዲያውም የሰባ ወይፈንን አመጣ፡፡ አል ዛሪያት - Aya 26
فَقَرَّبَهُ إِلَيْهِمْ قَالَ أَلَا تَأْكُلُونَ ( 27 ) አል ዛሪያት - Aya 27
ወደእነርሱም (አርዶና ጠብሶ) አቀረበው፡፡ «አትበሉም ወይ?» አላቸው፡፡ አል ዛሪያት - Aya 27
فَأَوْجَسَ مِنْهُمْ خِيفَةً ۖ قَالُوا لَا تَخَفْ ۖ وَبَشَّرُوهُ بِغُلَامٍ عَلِيمٍ ( 28 ) አል ዛሪያት - Aya 28
ከእነርሱ መፍራትንም በልቡ አሳደረ፡፡ «አትፍራ» አሉት፡፡ በዐዋቂ ወጣት ልጅም አበሰሩት፡፡ አል ዛሪያት - Aya 28
فَأَقْبَلَتِ امْرَأَتُهُ فِي صَرَّةٍ فَصَكَّتْ وَجْهَهَا وَقَالَتْ عَجُوزٌ عَقِيمٌ ( 29 ) አል ዛሪያት - Aya 29
ሚስቱም እየጮኸች መጣች፡፡ ፊቷንም መታች፡፡ «መካን አሮጊት ነኝ» አለችም፡፡ አል ዛሪያት - Aya 29
قَالُوا كَذَٰلِكِ قَالَ رَبُّكِ ۖ إِنَّهُ هُوَ الْحَكِيمُ الْعَلِيمُ ( 30 ) አል ዛሪያት - Aya 30
እንደዚህ ጌታሽ ብሏል፡፡ «እነሆ እርሱ ጥበባ ዐዋቂ ነውና» አሏት፡፡ አል ዛሪያት - Aya 30
قَالَ فَمَا خَطْبُكُمْ أَيُّهَا الْمُرْسَلُونَ ( 31 ) አል ዛሪያት - Aya 31
«እናንተ መልክተኞች ሆይ! ታዲያ ነገራችሁ ምንድን ነው?» አላቸው፡፡ አል ዛሪያት - Aya 31
قَالُوا إِنَّا أُرْسِلْنَا إِلَىٰ قَوْمٍ مُّجْرِمِينَ ( 32 ) አል ዛሪያት - Aya 32
(እነርሱም) አሉ፡- «እኛ ወደ አመጸኞች ሕዝቦች ተልከናል፡፡» አል ዛሪያት - Aya 32
لِنُرْسِلَ عَلَيْهِمْ حِجَارَةً مِّن طِينٍ ( 33 ) አል ዛሪያት - Aya 33
በእነርሱ ላይ ከጭቃ የኾኑን ድንጋዮች ልንለቅባቸው (ተላክን)፡፡ አል ዛሪያት - Aya 33
مُّسَوَّمَةً عِندَ رَبِّكَ لِلْمُسْرِفِينَ ( 34 ) አል ዛሪያት - Aya 34
በጌታህ ዘንድ ለድንበር አላፊዎቹ (በየስማቸው) ምልክት የተደረገባት ስትኾን፡፡ አል ዛሪያት - Aya 34
فَأَخْرَجْنَا مَن كَانَ فِيهَا مِنَ الْمُؤْمِنِينَ ( 35 ) አል ዛሪያት - Aya 35
ከምእምናንም፤ በእርሷ (በከተማቸው) ውስጥ የነበሩትን አወጣን፡፡ አል ዛሪያት - Aya 35
فَمَا وَجَدْنَا فِيهَا غَيْرَ بَيْتٍ مِّنَ الْمُسْلِمِينَ ( 36 ) አል ዛሪያት - Aya 36
በውስጧም ከሙስሊሞች ከአንድ ቤት (ቤተሰቦች) በስተቀር አላገኘንም፡፡ አል ዛሪያት - Aya 36
وَتَرَكْنَا فِيهَا آيَةً لِّلَّذِينَ يَخَافُونَ الْعَذَابَ الْأَلِيمَ ( 37 ) አል ዛሪያት - Aya 37
በውስጧም ለእነዚያ አሳማሚውን ቅጣት ለሚፈሩት ምልክትን አስቀረን፡፡ አል ዛሪያት - Aya 37
وَفِي مُوسَىٰ إِذْ أَرْسَلْنَاهُ إِلَىٰ فِرْعَوْنَ بِسُلْطَانٍ مُّبِينٍ ( 38 ) አል ዛሪያት - Aya 38
በሙሳም (ወሬ) ውስጥ ወደ ፈርዖን በግልጽ ማስረጃ በላክነው ጊዜ (ምልክትን አደረግን)፡፡ አል ዛሪያት - Aya 38
فَتَوَلَّىٰ بِرُكْنِهِ وَقَالَ سَاحِرٌ أَوْ مَجْنُونٌ ( 39 ) አል ዛሪያት - Aya 39
ከድጋፉ (ከሰራዊቱ) ጋርም (ከእምነት) ዞረ፡፡ (እርሱ) «ድግምተኛ ወይም ዕብድ ነው» አለም፡፡ አል ዛሪያት - Aya 39
فَأَخَذْنَاهُ وَجُنُودَهُ فَنَبَذْنَاهُمْ فِي الْيَمِّ وَهُوَ مُلِيمٌ ( 40 ) አል ዛሪያት - Aya 40
እርሱንም ሰራዊቱንም ያዝናቸው፡፡ እርሱ ተወቃሽ ሲኾን በባሕር ውስጥም ጣልናቸው፡፡ አል ዛሪያት - Aya 40
وَفِي عَادٍ إِذْ أَرْسَلْنَا عَلَيْهِمُ الرِّيحَ الْعَقِيمَ ( 41 ) አል ዛሪያት - Aya 41
በዓድም በእነርሱ ላይ መካንን ነፋስ በላክን ጊዜ (ምልክት አልለ)፡፡ አል ዛሪያት - Aya 41
مَا تَذَرُ مِن شَيْءٍ أَتَتْ عَلَيْهِ إِلَّا جَعَلَتْهُ كَالرَّمِيمِ ( 42 ) አል ዛሪያት - Aya 42
በላዩ ላይ የመጣችበትን ማንኛውንም ነገር እንደ በሰበሰ አጥንት ያደረገችው ብትኾን እንጂ አትተወውም፡፡ አል ዛሪያት - Aya 42
وَفِي ثَمُودَ إِذْ قِيلَ لَهُمْ تَمَتَّعُوا حَتَّىٰ حِينٍ ( 43 ) አል ዛሪያት - Aya 43
በሰሙድም ለእነርሱ «እስከ ጊዜ (ሞታችሁ) ድረስ ተጣቀሙ» በተባሉ ጊዜ (ምልክት አልለ)፡፡ አል ዛሪያት - Aya 43
فَعَتَوْا عَنْ أَمْرِ رَبِّهِمْ فَأَخَذَتْهُمُ الصَّاعِقَةُ وَهُمْ يَنظُرُونَ ( 44 ) አል ዛሪያት - Aya 44
ከጌታቸው ትዕዛዝም ኮሩ፡፡ እነርሱም እያዩ ጩኸት ያዘቻቸው፡፡ አል ዛሪያት - Aya 44
فَمَا اسْتَطَاعُوا مِن قِيَامٍ وَمَا كَانُوا مُنتَصِرِينَ ( 45 ) አል ዛሪያት - Aya 45
መቆምንም ምንም አልቻሉም፡፡ የሚርረዱም አልነበሩም፡፡ አል ዛሪያት - Aya 45
وَقَوْمَ نُوحٍ مِّن قَبْلُ ۖ إِنَّهُمْ كَانُوا قَوْمًا فَاسِقِينَ ( 46 ) አል ዛሪያት - Aya 46
የኑሕንም ሕዝቦች ከዚህ በፊት (አጠፋን)፡፡ እነርሱ አመጸኞች ሕዝቦች ነበሩና፡፡ አል ዛሪያት - Aya 46
وَالسَّمَاءَ بَنَيْنَاهَا بِأَيْدٍ وَإِنَّا لَمُوسِعُونَ ( 47 ) አል ዛሪያት - Aya 47
ሰማይንም በኀይል ገነባናት፡፡ እኛም በእርግጥ ቻዮች ነን፡፡ አል ዛሪያት - Aya 47
وَالْأَرْضَ فَرَشْنَاهَا فَنِعْمَ الْمَاهِدُونَ ( 48 ) አል ዛሪያት - Aya 48
ምድርንም ዘረጋናት፡፡ ምን ያማርንም ዘርጊዎች (ነን!) አል ዛሪያት - Aya 48
وَمِن كُلِّ شَيْءٍ خَلَقْنَا زَوْجَيْنِ لَعَلَّكُمْ تَذَكَّرُونَ ( 49 ) አል ዛሪያት - Aya 49
ትገነዘቡም ዘንድ ከነገሩ ሁሉ ሁለት (ተቃራኒ) ዓይነትን ፈጠርን፡፡ አል ዛሪያት - Aya 49
فَفِرُّوا إِلَى اللَّهِ ۖ إِنِّي لَكُم مِّنْهُ نَذِيرٌ مُّبِينٌ ( 50 ) አል ዛሪያት - Aya 50
«ወደ አላህም ሽሹ፤ እኔ ለእናንተ ከርሱ ግልጽ አስጠንቃቂ ነኝና» (በላቸው)፡፡ አል ዛሪያት - Aya 50
وَلَا تَجْعَلُوا مَعَ اللَّهِ إِلَٰهًا آخَرَ ۖ إِنِّي لَكُم مِّنْهُ نَذِيرٌ مُّبِينٌ ( 51 ) አል ዛሪያት - Aya 51
ከአላህም ጋር ሌላን አምላክ አታድርጉ፡፡ እኔ ለእናንተ ከእርሱ (የተላክሁ) ግልጽ አስፈራሪ ነኝና፡፡ አል ዛሪያት - Aya 51
كَذَٰلِكَ مَا أَتَى الَّذِينَ مِن قَبْلِهِم مِّن رَّسُولٍ إِلَّا قَالُوا سَاحِرٌ أَوْ مَجْنُونٌ ( 52 ) አል ዛሪያት - Aya 52
(ነገሩ) እንደዚሁ ነው፡፡ እነዚያን ከእነርሱ በፊት የነበሩትን ከመልክተኛ ማንም አልመጣቸውም፡፡ (እርሱ) «ድግምተኛ ወይም ዕብድ ነው» ያሉ ቢኾኑ እንጂ፡፡ አል ዛሪያት - Aya 52
أَتَوَاصَوْا بِهِ ۚ بَلْ هُمْ قَوْمٌ طَاغُونَ ( 53 ) አል ዛሪያት - Aya 53
በእርሱ (በዚህ ቃል) አደራ ተባብለዋልን? አይደለም፤ እነርሱ ጥጋበኞች ሕዝቦች ናቸው፡፡ አል ዛሪያት - Aya 53
فَتَوَلَّ عَنْهُمْ فَمَا أَنتَ بِمَلُومٍ ( 54 ) አል ዛሪያት - Aya 54
ከእነርሱም (ክርክር) ዘወር በል፤ (ተዋቸው)፡፡ አንተ ምንም ተወቃሽ አይደለህምና፡፡ አል ዛሪያት - Aya 54
وَذَكِّرْ فَإِنَّ الذِّكْرَىٰ تَنفَعُ الْمُؤْمِنِينَ ( 55 ) አል ዛሪያት - Aya 55
ገሥጽም፤ ግሣጼ ምእመናንን ትጠቅማለችና፡፡ አል ዛሪያት - Aya 55
وَمَا خَلَقْتُ الْجِنَّ وَالْإِنسَ إِلَّا لِيَعْبُدُونِ ( 56 ) አል ዛሪያት - Aya 56
ጋኔንንና ሰውንም ሊግገዙኝ እንጅ ለሌላ አልፈጠርኳቸውም፡፡ አል ዛሪያት - Aya 56
مَا أُرِيدُ مِنْهُم مِّن رِّزْقٍ وَمَا أُرِيدُ أَن يُطْعِمُونِ ( 57 ) አል ዛሪያት - Aya 57
ከነርሱም ምንም ሲሳይ አልፈልግም፡፡ ሊመግቡኝም አልሻም፡፡ አል ዛሪያት - Aya 57
إِنَّ اللَّهَ هُوَ الرَّزَّاقُ ذُو الْقُوَّةِ الْمَتِينُ ( 58 ) አል ዛሪያት - Aya 58
አላህ እርሱ ሲሳይን ሰጪ የብርቱ ኀይል ባለቤት ነው፡፡ አል ዛሪያት - Aya 58
فَإِنَّ لِلَّذِينَ ظَلَمُوا ذَنُوبًا مِّثْلَ ذَنُوبِ أَصْحَابِهِمْ فَلَا يَسْتَعْجِلُونِ ( 59 ) አል ዛሪያት - Aya 59
ለእነዚያም ለበደሉት እንደ ጓደኞቻቸው ፋንታ ብጤ (የቅጣት) ፋንታ አልላቸው፡፡ ስለዚህ አያስቸኩሉኝ፡፡ አል ዛሪያት - Aya 59
فَوَيْلٌ لِّلَّذِينَ كَفَرُوا مِن يَوْمِهِمُ الَّذِي يُوعَدُونَ ( 60 ) አል ዛሪያት - Aya 60
ለነዚያም ለካዱት ከዚያ ከሚቀጠሩት ቀናቸው ወዮላቸው፡ አል ዛሪያት - Aya 60
Facebook Twitter Google+ Pinterest Reddit StumbleUpon Linkedin Tumblr Google Bookmarks Email

Select Translation

Select surah