አማርኛ Muhammad Sadiq & Sani Habib
Surah አል ሙርሰላ - Aya count 50
وَالْمُرْسَلَاتِ عُرْفًا
( 1 ) 
ተከታታይ ኾነው በተላኩት፣

فَالْعَاصِفَاتِ عَصْفًا
( 2 ) 
በኀይል መንፈስን ነፋሾች በኾኑትም፣

وَالنَّاشِرَاتِ نَشْرًا
( 3 ) 
መበተንን በታኞች በኾኑትም፤ (ነፋሶች)፣

فَالْفَارِقَاتِ فَرْقًا
( 4 ) 
መለየትን ለይዎች በኾኑትም፣

فَالْمُلْقِيَاتِ ذِكْرًا
( 5 ) 
መገሠጫን (ወደ ነቢያት) ጣይዎች በኾኑትም፣

عُذْرًا أَوْ نُذْرًا
( 6 ) 
ምክንያትን ለማስወገድ ወይም ለማስፈራራት (ጣይዎች በኾኑት መላእክት) እምላለሁ፡፡

إِنَّمَا تُوعَدُونَ لَوَاقِعٌ
( 7 ) 
ያ የምትስፈራሩበት (ትንሣኤ) በእርግጥ ኋኝ ነው፡፡

فَإِذَا النُّجُومُ طُمِسَتْ
( 8 ) 
ከዋክብትም (ብርሃንዋ) በታበሰች ጊዜ፡፡

وَإِذَا السَّمَاءُ فُرِجَتْ
( 9 ) 
ሰማይም በተከፈተች ጊዜ፡፡

وَإِذَا الْجِبَالُ نُسِفَتْ
( 10 ) 
ጋራዎችም በተንኮተኮቱ ጊዜ፡፡

وَإِذَا الرُّسُلُ أُقِّتَتْ
( 11 ) 
መልክተኞቹም ወቅት በተደረገላቸው ጊዜ፡፡

لِأَيِّ يَوْمٍ أُجِّلَتْ
( 12 ) 
ለየትኛው ቀን ተቀጠሩ (የሚባል ሲኾን)፤

لِيَوْمِ الْفَصْلِ
( 13 ) 
ለመለያው ቀን (በተባለ ጊዜ፤ በፍጡሮች መካከል ይፈረዳል)፡፡

وَمَا أَدْرَاكَ مَا يَوْمُ الْفَصْلِ
( 14 ) 
የመለያውም ቀን ምን እንደኾነ ምን አሳወቀህ?

وَيْلٌ يَوْمَئِذٍ لِّلْمُكَذِّبِينَ
( 15 ) 
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

أَلَمْ نُهْلِكِ الْأَوَّلِينَ
( 16 ) 
የፊተኞቹን (ሕዝቦች) አላጠፋንምን?

ثُمَّ نُتْبِعُهُمُ الْآخِرِينَ
( 17 ) 
ከዚያም የኋለኞቹን እናስከትላቸዋለን፡፡

كَذَٰلِكَ نَفْعَلُ بِالْمُجْرِمِينَ
( 18 ) 
በአመጸኞች ሁሉ እንደዚሁ እንሠራለን፡፡

وَيْلٌ يَوْمَئِذٍ لِّلْمُكَذِّبِينَ
( 19 ) 
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

أَلَمْ نَخْلُقكُّم مِّن مَّاءٍ مَّهِينٍ
( 20 ) 
ከደካማ ውሃ አልፈጠርናችሁምን?

فَجَعَلْنَاهُ فِي قَرَارٍ مَّكِينٍ
( 21 ) 
በተጠበቀ መርጊያ ውስጥም (በማሕፀን) አደረግነው፡፡

إِلَىٰ قَدَرٍ مَّعْلُومٍ
( 22 ) 
እስከ ታወቀ ልክ ድረስ፡፡ መጠንነውም፤ ምን ያማርንም

فَقَدَرْنَا فَنِعْمَ الْقَادِرُونَ
( 23 ) 
መጣኞች ነን!

وَيْلٌ يَوْمَئِذٍ لِّلْمُكَذِّبِينَ
( 24 ) 
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

أَلَمْ نَجْعَلِ الْأَرْضَ كِفَاتًا
( 25 ) 
ምድርን ሰብሳቢ አላደረግናትምን?

أَحْيَاءً وَأَمْوَاتًا
( 26 ) 
ሕያዋን ኾናችሁ ሙታንም ኾናችሁ፡፡

وَجَعَلْنَا فِيهَا رَوَاسِيَ شَامِخَاتٍ وَأَسْقَيْنَاكُم مَّاءً فُرَاتًا
( 27 ) 
በውስጧም ከፍተኛዎችን ተራራዎች አደረግን፡፡ ጣፋጭ ውሃንም አጠጣናችሁ፡፡

وَيْلٌ يَوْمَئِذٍ لِّلْمُكَذِّبِينَ
( 28 ) 
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

انطَلِقُوا إِلَىٰ مَا كُنتُم بِهِ تُكَذِّبُونَ
( 29 ) 
«ወደዚያ በእርሱ ታስተባብሉ ወደ ነበራችሁት (ቅጣት) አዝግሙ፡፡

انطَلِقُوا إِلَىٰ ظِلٍّ ذِي ثَلَاثِ شُعَبٍ
( 30 ) 
«ባለ ሦስት ቅርንጫፎች ወደ ኾነው ጥላ አዝግሙ፤» (ይባላሉ)፡፡

لَّا ظَلِيلٍ وَلَا يُغْنِي مِنَ اللَّهَبِ
( 31 ) 
አጠላይ ያልኾነ ከእሳቱም ላንቃ የማያድን ወደ ኾነው (አዝግሙ)፡፡

إِنَّهَا تَرْمِي بِشَرَرٍ كَالْقَصْرِ
( 32 ) 
እርሷ እንደ ታላላቅ ሕንጻ የኾኑን ቃንቄዎች ትወረውራለች፡፡

كَأَنَّهُ جِمَالَتٌ صُفْرٌ
( 33 ) 
(ቃንቄውም) ልክ ዳለቻዎች ግመሎችን ይመስላል፡፡

وَيْلٌ يَوْمَئِذٍ لِّلْمُكَذِّبِينَ
( 34 ) 
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

هَٰذَا يَوْمُ لَا يَنطِقُونَ
( 35 ) 
ይህ የማይናገሩበት ቀን ነው፡፡

وَلَا يُؤْذَنُ لَهُمْ فَيَعْتَذِرُونَ
( 36 ) 
ይቅርታም ይጠይቁ ዘንድ፤ ለእነርሱ አይፈቀድላቸውም፡፡

وَيْلٌ يَوْمَئِذٍ لِّلْمُكَذِّبِينَ
( 37 ) 
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

هَٰذَا يَوْمُ الْفَصْلِ ۖ جَمَعْنَاكُمْ وَالْأَوَّلِينَ
( 38 ) 
ይህ መለያው ቀን ነው፡፡ እናንተንም የፊተኞቹንም ሰብሰብናችሁ፡፡

فَإِن كَانَ لَكُمْ كَيْدٌ فَكِيدُونِ
( 39 ) 
ለናንተም (ለማምለጥ) ብልሃት እንዳላችሁ ተተናኮሉኝ፡፡

وَيْلٌ يَوْمَئِذٍ لِّلْمُكَذِّبِينَ
( 40 ) 
ላስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

إِنَّ الْمُتَّقِينَ فِي ظِلَالٍ وَعُيُونٍ
( 41 ) 
ጥንቁቆቹ በጥላዎችና በምንጮች ውስጥ ናቸው፡፡

وَفَوَاكِهَ مِمَّا يَشْتَهُونَ
( 42 ) 
ከሚከጅሉትም ሁሉ በፍራፍሬዎች ውስጥ ናቸው፡፡

كُلُوا وَاشْرَبُوا هَنِيئًا بِمَا كُنتُمْ تَعْمَلُونَ
( 43 ) 
«ትሠሩት በነበራችሁት ዋጋ የምትደሰቱ ኾናችሁ ብሉ፣ ጠጡም፤» (ይባላሉ)፡፡

إِنَّا كَذَٰلِكَ نَجْزِي الْمُحْسِنِينَ
( 44 ) 
እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡

وَيْلٌ يَوْمَئِذٍ لِّلْمُكَذِّبِينَ
( 45 ) 
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

كُلُوا وَتَمَتَّعُوا قَلِيلًا إِنَّكُم مُّجْرِمُونَ
( 46 ) 
ብሉ፤ ጥቂትንም (ጊዜ) ተጠቀሙ፡፡ እናንተ አመጸኞች ናችሁና፡፡

وَيْلٌ يَوْمَئِذٍ لِّلْمُكَذِّبِينَ
( 47 ) 
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

وَإِذَا قِيلَ لَهُمُ ارْكَعُوا لَا يَرْكَعُونَ
( 48 ) 
«ለእነርሱ ስገዱም» በተባሉ ጊዜ አይሰግዱም፡፡

وَيْلٌ يَوْمَئِذٍ لِّلْمُكَذِّبِينَ
( 49 ) 
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

فَبِأَيِّ حَدِيثٍ بَعْدَهُ يُؤْمِنُونَ
( 50 ) 
ከእርሱም ሌላ በየትኛው ንግግር ያምናሉ?
