አማርኛ Muhammad Sadiq & Sani Habib
Surah አል ቂያማህ - Aya count 40
لَا أُقْسِمُ بِيَوْمِ الْقِيَامَةِ
( 1 ) 
(ነገሩ ከሓዲዎች እንደሚሉት) አይደለም፡፡ በትንሣኤ ቀን እምላለሁ፡፡

وَلَا أُقْسِمُ بِالنَّفْسِ اللَّوَّامَةِ
( 2 ) 
(ራሷን) ወቃሽ በኾነች ነፍስም እምላለሁ፡፡ (በእርግጥ ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡

أَيَحْسَبُ الْإِنسَانُ أَلَّن نَّجْمَعَ عِظَامَهُ
( 3 ) 
ሰው አጥንቶቹን አለመሰብሰባችንን ያስባልን?

بَلَىٰ قَادِرِينَ عَلَىٰ أَن نُّسَوِّيَ بَنَانَهُ
( 4 ) 
አይደለም ጣቶቹን (ፊት እንደ ነበሩ) በማስተካከል ላይ ቻዮች ስንኾን (እንሰበስባቸዋለን)፡፡

بَلْ يُرِيدُ الْإِنسَانُ لِيَفْجُرَ أَمَامَهُ
( 5 ) 
ይልቁንም ሰው በፊቱ ባለው ነገር (በትንሣኤ) ሊያስተባብል ይፈልጋል፡፡

يَسْأَلُ أَيَّانَ يَوْمُ الْقِيَامَةِ
( 6 ) 
«የትንሣኤው ቀን መቼ ነው?» ሲል ይጠይቃል፡፡

فَإِذَا بَرِقَ الْبَصَرُ
( 7 ) 
ዓይንም በዋለለ ጊዜ፡፡

وَخَسَفَ الْقَمَرُ
( 8 ) 
ጨረቃም በጨለመ ጊዜ፡፡

وَجُمِعَ الشَّمْسُ وَالْقَمَرُ
( 9 ) 
ፀሐይና ጨረቃም በተሰበሰቡ ጊዜ፡፡

يَقُولُ الْإِنسَانُ يَوْمَئِذٍ أَيْنَ الْمَفَرُّ
( 10 ) 
«ሰው በዚያ ቀን መሸሻው የት ነው?» ይላል፡፡

كَلَّا لَا وَزَرَ
( 11 ) 
ይከልከል፤ ምንም መጠጊያ የለም፡፡

إِلَىٰ رَبِّكَ يَوْمَئِذٍ الْمُسْتَقَرُّ
( 12 ) 
በዚያ ቀን መርጊያው ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡

يُنَبَّأُ الْإِنسَانُ يَوْمَئِذٍ بِمَا قَدَّمَ وَأَخَّرَ
( 13 ) 
ሰው በዚያ ቀን ባስቀደመውና ባስቆየው ሁሉ ይነገራል፡፡

بَلِ الْإِنسَانُ عَلَىٰ نَفْسِهِ بَصِيرَةٌ
( 14 ) 
በእርግጥም ሰው በነፍሱ ላይ አስረጅ ነው፡፡ (አካሎቹ ይመሰክሩበታል)፡፡

وَلَوْ أَلْقَىٰ مَعَاذِيرَهُ
( 15 ) 
ምክንያቶቹን ሁሉ ቢያመጣም እንኳ (አይሰማም)፡፡

لَا تُحَرِّكْ بِهِ لِسَانَكَ لِتَعْجَلَ بِهِ
( 16 ) 
በእርሱ (በቁርኣን ንባብ) ልትቸኩል ምላስህን በእርሱ አታላውስ፡፡

إِنَّ عَلَيْنَا جَمْعَهُ وَقُرْآنَهُ
( 17 ) 
(በልብህ ውስጥ) መሰብሰቡና ማንበቡ በእኛ ላይ ነውና፡፡

فَإِذَا قَرَأْنَاهُ فَاتَّبِعْ قُرْآنَهُ
( 18 ) 
ባነበብነውም ጊዜ (ካለቀ በኋላ) ንባቡን ተከተል፡፡

ثُمَّ إِنَّ عَلَيْنَا بَيَانَهُ
( 19 ) 
ከዚያም ማብራራቱ በእኛ ላይ ነው፡፡

كَلَّا بَلْ تُحِبُّونَ الْعَاجِلَةَ
( 20 ) 
(ከመጣደፍ) ተከልከል፡፡ ይልቁንም (ሰዎች) ፈጣኒቱን (ዓለም) ትወዳላችሁ፡፡

وَتَذَرُونَ الْآخِرَةَ
( 21 ) 
መጨረሻይቱንም (ዓለም) ትተዋላችሁ፡፡ (አትዘጋጁላትም)፡፡

وُجُوهٌ يَوْمَئِذٍ نَّاضِرَةٌ
( 22 ) 
ፊቶች በዚያ ቀን አብሪዎች ናቸው፡፡

إِلَىٰ رَبِّهَا نَاظِرَةٌ
( 23 ) 
ወደ ጌታቸው ተመልካቾች ናቸው፡፡

وَوُجُوهٌ يَوْمَئِذٍ بَاسِرَةٌ
( 24 ) 
ፊቶችም በዚያ ቀን ጨፍጋጊዎች ናቸው፡፡

تَظُنُّ أَن يُفْعَلَ بِهَا فَاقِرَةٌ
( 25 ) 
በርሳቸውም ዐደጋ እንደሚሠራባቸው ያረጋግጣሉ፡፡

كَلَّا إِذَا بَلَغَتِ التَّرَاقِيَ
( 26 ) 
ንቁ (ነፍስ) ብሪዎችን በደረሰች ጊዜ፤

وَقِيلَ مَنْ ۜ رَاقٍ
( 27 ) 
«አሻሪው ማነው?» በተባለም ጊዜ፡፡

وَظَنَّ أَنَّهُ الْفِرَاقُ
( 28 ) 
(ሕመምተኛው) እርሱ (የሰፈረበት ነገር ከዚህ ዓለም) መልለየት መኾኑን ባረጋገጠም ጊዜ፡፡

وَالْتَفَّتِ السَّاقُ بِالسَّاقِ
( 29 ) 
ባትም በባት በተጣበቀች ጊዜ፡፡

إِلَىٰ رَبِّكَ يَوْمَئِذٍ الْمَسَاقُ
( 30 ) 
በዚያ ቀን መነዳቱ ወደ ጌታህ (ፍርድ) ነው፡፡

فَلَا صَدَّقَ وَلَا صَلَّىٰ
( 31 ) 
አላመነምም አልሰገደምም፡፡

وَلَٰكِن كَذَّبَ وَتَوَلَّىٰ
( 32 ) 
ግን አስተባበለ፤ (ከእምነት) ዞረም፡፡

ثُمَّ ذَهَبَ إِلَىٰ أَهْلِهِ يَتَمَطَّىٰ
( 33 ) 
ከዚያም እየተንጎባለለ ወደ ቤተሰቡ ኼደ፡፡

أَوْلَىٰ لَكَ فَأَوْلَىٰ
( 34 ) 
የምትጠላውን ነገር (አላህ) ያስከትልህ፡፡ ለአንተ ተገቢህም ነው፡፡

ثُمَّ أَوْلَىٰ لَكَ فَأَوْلَىٰ
( 35 ) 
ከዚያም ጥፋት ይጠጋህ ለአንተ የተገባህም ነው፡፡

أَيَحْسَبُ الْإِنسَانُ أَن يُتْرَكَ سُدًى
( 36 ) 
ሰው ስድ ኾኖ መትተውን ይጠረጥራልን?

أَلَمْ يَكُ نُطْفَةً مِّن مَّنِيٍّ يُمْنَىٰ
( 37 ) 
የሚፈሰስ ከኾነ የፍትወት ጠብታ አልነበረምን?

ثُمَّ كَانَ عَلَقَةً فَخَلَقَ فَسَوَّىٰ
( 38 ) 
ከዚያም የረጋ ደም ኾነ (አላህ ሰው አድርጎ) ፈጠረውም፡፡ አስተካከለውም፡፡

فَجَعَلَ مِنْهُ الزَّوْجَيْنِ الذَّكَرَ وَالْأُنثَىٰ
( 39 ) 
ከእርሱም ሁለት ዓይነቶችን ወንድና ሴትን አደረገ፡፡

أَلَيْسَ ذَٰلِكَ بِقَادِرٍ عَلَىٰ أَن يُحْيِيَ الْمَوْتَىٰ
( 40 ) 
ይህ (ጌታ) ሙታንን ሕያው በማድረግ ላይ ቻይ አይደለምን?
