Surah አል መዓሪጅ

አማርኛ Muhammad Sadiq & Sani Habib

Surah አል መዓሪጅ - Aya count 44
Facebook Twitter Google+ Pinterest Reddit StumbleUpon Linkedin Tumblr Google Bookmarks Email
سَأَلَ سَائِلٌ بِعَذَابٍ وَاقِعٍ ( 1 ) አል መዓሪጅ - Aya 1
ወዳቂ ከኾነው ቅጣት ጠያቂ ጠየቀ፡፡ አል መዓሪጅ - Aya 1
لِّلْكَافِرِينَ لَيْسَ لَهُ دَافِعٌ ( 2 ) አል መዓሪጅ - Aya 2
በከሓዲዎች ላይ (ወዳቂ ከኾነው) ለእርሱ መላሽ የለውም፡፡ አል መዓሪጅ - Aya 2
مِّنَ اللَّهِ ذِي الْمَعَارِجِ ( 3 ) አል መዓሪጅ - Aya 3
የ(ሰማያት) መሰላሎች ባለቤት ከኾነው አላህ (መላሽ የለውም)፡፡ አል መዓሪጅ - Aya 3
تَعْرُجُ الْمَلَائِكَةُ وَالرُّوحُ إِلَيْهِ فِي يَوْمٍ كَانَ مِقْدَارُهُ خَمْسِينَ أَلْفَ سَنَةٍ ( 4 ) አል መዓሪጅ - Aya 4
መላእክቱና መንፈሱም ልኩ አምሳ ሺሕ ዓመት በኾነ ቀን ውስጥ ወደእርሱ ያርጋሉ፤ (ይወጣሉ)፡፡ አል መዓሪጅ - Aya 4
فَاصْبِرْ صَبْرًا جَمِيلًا ( 5 ) አል መዓሪጅ - Aya 5
መልካምንም ትዕግስት ታገሥ፡፡ አል መዓሪጅ - Aya 5
إِنَّهُمْ يَرَوْنَهُ بَعِيدًا ( 6 ) አል መዓሪጅ - Aya 6
እነርሱ (ያንን ቀን) ሩቅ አድርገው ያዩታል፡፡ አል መዓሪጅ - Aya 6
وَنَرَاهُ قَرِيبًا ( 7 ) አል መዓሪጅ - Aya 7
እኛም ቅርብ ኾኖ እናየዋለን፡፡ አል መዓሪጅ - Aya 7
يَوْمَ تَكُونُ السَّمَاءُ كَالْمُهْلِ ( 8 ) አል መዓሪጅ - Aya 8
ሰማይ እንደ ዘይት አተላ በምትኾንበት ቀን፡፡ አል መዓሪጅ - Aya 8
وَتَكُونُ الْجِبَالُ كَالْعِهْنِ ( 9 ) አል መዓሪጅ - Aya 9
ጋራዎችም በተለያዩ ቀለማት እንደ ተነከረ ሱፍ (ነፋስ እንደሚያበረው) በሚኾኑበት ቀን፡፡ አል መዓሪጅ - Aya 9
وَلَا يَسْأَلُ حَمِيمٌ حَمِيمًا ( 10 ) አል መዓሪጅ - Aya 10
ዘመድም ዘመድን በማይጠይቅበት ቀን፤ (መላሽ የለውም)፡፡ አል መዓሪጅ - Aya 10
يُبَصَّرُونَهُمْ ۚ يَوَدُّ الْمُجْرِمُ لَوْ يَفْتَدِي مِنْ عَذَابِ يَوْمِئِذٍ بِبَنِيهِ ( 11 ) አል መዓሪጅ - Aya 11
(ዘመዶቻቸውን) ያዩዋቸዋል፡፡ አመጸኛው ከዚያ ቀን ስቃይ (ነፍሱን) በልጆቹ ሊበዥ ይመኛል፡፡ አል መዓሪጅ - Aya 11
وَصَاحِبَتِهِ وَأَخِيهِ ( 12 ) አል መዓሪጅ - Aya 12
በሚስቱም በወንድሙም፡፡ አል መዓሪጅ - Aya 12
وَفَصِيلَتِهِ الَّتِي تُؤْوِيهِ ( 13 ) አል መዓሪጅ - Aya 13
በዚያችም በምታስጠጋው ጎሳው፡፡ አል መዓሪጅ - Aya 13
وَمَن فِي الْأَرْضِ جَمِيعًا ثُمَّ يُنجِيهِ ( 14 ) አል መዓሪጅ - Aya 14
በምድርም ላይ ባለው ሁሉ (ሊበዥ) ከዚያም ሊያድነው (ይመኛል)፡፡ አል መዓሪጅ - Aya 14
كَلَّا ۖ إِنَّهَا لَظَىٰ ( 15 ) አል መዓሪጅ - Aya 15
ይተው! እርሷ (እሳቲቱ) ለዟ ናት፡፡ አል መዓሪጅ - Aya 15
نَزَّاعَةً لِّلشَّوَىٰ ( 16 ) አል መዓሪጅ - Aya 16
የራስን ቅል ቆዳ የምትሞሽልቅ ስትኾን፡፡ አል መዓሪጅ - Aya 16
تَدْعُو مَنْ أَدْبَرَ وَتَوَلَّىٰ ( 17 ) አል መዓሪጅ - Aya 17
(ከእምነት) የዞረንና የሸሸን ሰው (ወደእርሷ) ትጠራለች፡፡ አል መዓሪጅ - Aya 17
وَجَمَعَ فَأَوْعَىٰ ( 18 ) አል መዓሪጅ - Aya 18
ገንዘብን የሰበሰበንና (ዘካውን ሳይሰጥ) የቆጠረንም፤ (ትጠራለች)፡፡ አል መዓሪጅ - Aya 18
إِنَّ الْإِنسَانَ خُلِقَ هَلُوعًا ( 19 ) አል መዓሪጅ - Aya 19
ሰው ቅጠ ቢስ ኾኖ ተፈጠረ፡፡ አል መዓሪጅ - Aya 19
إِذَا مَسَّهُ الشَّرُّ جَزُوعًا ( 20 ) አል መዓሪጅ - Aya 20
ክፉ ነገር ባገኘው ጊዜ ብስጪተኛ፡፡ አል መዓሪጅ - Aya 20
وَإِذَا مَسَّهُ الْخَيْرُ مَنُوعًا ( 21 ) አል መዓሪጅ - Aya 21
መልካምም ነገር (ድሎት) ባገኘ ጊዜ ከልካይ (ኾኖ ተፈጠረ)፡፡ አል መዓሪጅ - Aya 21
إِلَّا الْمُصَلِّينَ ( 22 ) አል መዓሪጅ - Aya 22
ሰጋጆቹ ብቻ ሲቀሩ፡፡ አል መዓሪጅ - Aya 22
الَّذِينَ هُمْ عَلَىٰ صَلَاتِهِمْ دَائِمُونَ ( 23 ) አል መዓሪጅ - Aya 23
እነዚያ እነርሱ በስግደታቸው ላይ ዘውታሪዎች የኾኑት፡፡ አል መዓሪጅ - Aya 23
وَالَّذِينَ فِي أَمْوَالِهِمْ حَقٌّ مَّعْلُومٌ ( 24 ) አል መዓሪጅ - Aya 24
እነዚያም በገንዘቦቻቸው ላይ የታወቀ መብት ያለባቸው የኾኑት፡፡ አል መዓሪጅ - Aya 24
لِّلسَّائِلِ وَالْمَحْرُومِ ( 25 ) አል መዓሪጅ - Aya 25
ለለማኝ ከልመና ለሚከለከልም (መብት ያለባቸው የኾኑት)፡፡ አል መዓሪጅ - Aya 25
وَالَّذِينَ يُصَدِّقُونَ بِيَوْمِ الدِّينِ ( 26 ) አል መዓሪጅ - Aya 26
እነዚያም በፍርዱ ቀን እውነት የሚሉት (የሚያረጋግጡት)፡፡ አል መዓሪጅ - Aya 26
وَالَّذِينَ هُم مِّنْ عَذَابِ رَبِّهِم مُّشْفِقُونَ ( 27 ) አል መዓሪጅ - Aya 27
እነዚያም እነርሱ ከጌታቸው ቅጣት ፈሪዎች የኾኑት፡፡ አል መዓሪጅ - Aya 27
إِنَّ عَذَابَ رَبِّهِمْ غَيْرُ مَأْمُونٍ ( 28 ) አል መዓሪጅ - Aya 28
የጌታቸው ቅጣት (መምጣቱ) የማያስተማምን ነውና፡፡ አል መዓሪጅ - Aya 28
وَالَّذِينَ هُمْ لِفُرُوجِهِمْ حَافِظُونَ ( 29 ) አል መዓሪጅ - Aya 29
እነዚያም እነርሱ ብልቶቻቸውን ጠባቂዎች የኾኑት፡፡ አል መዓሪጅ - Aya 29
إِلَّا عَلَىٰ أَزْوَاجِهِمْ أَوْ مَا مَلَكَتْ أَيْمَانُهُمْ فَإِنَّهُمْ غَيْرُ مَلُومِينَ ( 30 ) አል መዓሪጅ - Aya 30
በሚስቶቻቸው ወይም እጆቻቸው በያዙዋቸው (ባሪያዎች) ላይ ሲቀር፡፡ እነርሱ (በእነዚህ) የማይወቀሱ ናቸውና፡፡ አል መዓሪጅ - Aya 30
فَمَنِ ابْتَغَىٰ وَرَاءَ ذَٰلِكَ فَأُولَٰئِكَ هُمُ الْعَادُونَ ( 31 ) አል መዓሪጅ - Aya 31
ከዚያም ወዲያ የፈለገ ሰው እነዚያ እነሱ ድንበር አላፊዎች ናቸው፡፡ አል መዓሪጅ - Aya 31
وَالَّذِينَ هُمْ لِأَمَانَاتِهِمْ وَعَهْدِهِمْ رَاعُونَ ( 32 ) አል መዓሪጅ - Aya 32
እነዚያም እነርሱ አደራዎቻቸውንና ቃል ኪዳናቸውን ጠባቂዎች የኾኑት፡፡ አል መዓሪጅ - Aya 32
وَالَّذِينَ هُم بِشَهَادَاتِهِمْ قَائِمُونَ ( 33 ) አል መዓሪጅ - Aya 33
እነዚያም እነርሱ በምስክርነታቸው ትክክለኞች የኾኑት፡፡ አል መዓሪጅ - Aya 33
وَالَّذِينَ هُمْ عَلَىٰ صَلَاتِهِمْ يُحَافِظُونَ ( 34 ) አል መዓሪጅ - Aya 34
እነዚያም እነርሱ በሶላቶቻቸው ላይ የሚጠባበቁት፡፡ አል መዓሪጅ - Aya 34
أُولَٰئِكَ فِي جَنَّاتٍ مُّكْرَمُونَ ( 35 ) አል መዓሪጅ - Aya 35
እነዚህ (ከዚህ በላይ የተወሱት ሁሉ) በገነቶች ውስጥ የሚከበሩ ናቸው፡፡ አል መዓሪጅ - Aya 35
فَمَالِ الَّذِينَ كَفَرُوا قِبَلَكَ مُهْطِعِينَ ( 36 ) አል መዓሪጅ - Aya 36
ለእነዚያም ለካዱት ወደ አንተ በኩል አንገቶቻቸውን መዝዘው የሚያተኩሩት ምን አላቸው? አል መዓሪጅ - Aya 36
عَنِ الْيَمِينِ وَعَنِ الشِّمَالِ عِزِينَ ( 37 ) አል መዓሪጅ - Aya 37
ከቀኝና ከግራ ክፍልፍል ጭፍሮች ሲኾኑ፡፡ አል መዓሪጅ - Aya 37
أَيَطْمَعُ كُلُّ امْرِئٍ مِّنْهُمْ أَن يُدْخَلَ جَنَّةَ نَعِيمٍ ( 38 ) አል መዓሪጅ - Aya 38
ከእነርሱ እያንዳንዱ ሰው የጸጋይቱን ገነት መግባትን ይከጅላልን? አል መዓሪጅ - Aya 38
كَلَّا ۖ إِنَّا خَلَقْنَاهُم مِّمَّا يَعْلَمُونَ ( 39 ) አል መዓሪጅ - Aya 39
ይከልከል፤ እኛ ከሚያውቁት ነገር (ከፍቶት ጠብታ) ፈጠርናቸው፡፡ አል መዓሪጅ - Aya 39
فَلَا أُقْسِمُ بِرَبِّ الْمَشَارِقِ وَالْمَغَارِبِ إِنَّا لَقَادِرُونَ ( 40 ) አል መዓሪጅ - Aya 40
በምሥራቆችና በምዕራቦችም ጌታ እምላለሁ፡፡ እኛ በእርግጥ ቻዮች ነን፡፡ አል መዓሪጅ - Aya 40
عَلَىٰ أَن نُّبَدِّلَ خَيْرًا مِّنْهُمْ وَمَا نَحْنُ بِمَسْبُوقِينَ ( 41 ) አል መዓሪጅ - Aya 41
ከእነርሱ የተሻለን በመለወጥ ላይ፡፡ እኛም ተሸናፊዎች አይደለንም፡፡ አል መዓሪጅ - Aya 41
فَذَرْهُمْ يَخُوضُوا وَيَلْعَبُوا حَتَّىٰ يُلَاقُوا يَوْمَهُمُ الَّذِي يُوعَدُونَ ( 42 ) አል መዓሪጅ - Aya 42
ያንንም የሚስፈራሩበትን ቀናቸውን እስከሚገናኙ ድረስ ተዋቸው፡፡ ይዋኙ ይጫወቱም፡፡ አል መዓሪጅ - Aya 42
يَوْمَ يَخْرُجُونَ مِنَ الْأَجْدَاثِ سِرَاعًا كَأَنَّهُمْ إِلَىٰ نُصُبٍ يُوفِضُونَ ( 43 ) አል መዓሪጅ - Aya 43
ወደ ጣዖቶች እንደሚሽቀዳደሙ ኾነው ከመቃብሮቻቸው ፈጥነው የሚወጡበትን ቀን (እስከሚገናኙ ድረስ ተዋቸው)፡፡ አል መዓሪጅ - Aya 43
خَاشِعَةً أَبْصَارُهُمْ تَرْهَقُهُمْ ذِلَّةٌ ۚ ذَٰلِكَ الْيَوْمُ الَّذِي كَانُوا يُوعَدُونَ ( 44 ) አል መዓሪጅ - Aya 44
ዓይኖቻቸው ያፈሩ ኾነው ውርደት ትሸፍናቸዋለች፡፡ ይህ ቀን ያ ይስፈራሩበት የነበሩት ነው፡፡ አል መዓሪጅ - Aya 44
Facebook Twitter Google+ Pinterest Reddit StumbleUpon Linkedin Tumblr Google Bookmarks Email

Select Translation

Select surah