አማርኛ Muhammad Sadiq & Sani Habib
Surah አል መዓሪጅ - Aya count 44
سَأَلَ سَائِلٌ بِعَذَابٍ وَاقِعٍ
( 1 ) 
ወዳቂ ከኾነው ቅጣት ጠያቂ ጠየቀ፡፡

لِّلْكَافِرِينَ لَيْسَ لَهُ دَافِعٌ
( 2 ) 
በከሓዲዎች ላይ (ወዳቂ ከኾነው) ለእርሱ መላሽ የለውም፡፡

مِّنَ اللَّهِ ذِي الْمَعَارِجِ
( 3 ) 
የ(ሰማያት) መሰላሎች ባለቤት ከኾነው አላህ (መላሽ የለውም)፡፡

تَعْرُجُ الْمَلَائِكَةُ وَالرُّوحُ إِلَيْهِ فِي يَوْمٍ كَانَ مِقْدَارُهُ خَمْسِينَ أَلْفَ سَنَةٍ
( 4 ) 
መላእክቱና መንፈሱም ልኩ አምሳ ሺሕ ዓመት በኾነ ቀን ውስጥ ወደእርሱ ያርጋሉ፤ (ይወጣሉ)፡፡

فَاصْبِرْ صَبْرًا جَمِيلًا
( 5 ) 
መልካምንም ትዕግስት ታገሥ፡፡

إِنَّهُمْ يَرَوْنَهُ بَعِيدًا
( 6 ) 
እነርሱ (ያንን ቀን) ሩቅ አድርገው ያዩታል፡፡

وَنَرَاهُ قَرِيبًا
( 7 ) 
እኛም ቅርብ ኾኖ እናየዋለን፡፡

يَوْمَ تَكُونُ السَّمَاءُ كَالْمُهْلِ
( 8 ) 
ሰማይ እንደ ዘይት አተላ በምትኾንበት ቀን፡፡

وَتَكُونُ الْجِبَالُ كَالْعِهْنِ
( 9 ) 
ጋራዎችም በተለያዩ ቀለማት እንደ ተነከረ ሱፍ (ነፋስ እንደሚያበረው) በሚኾኑበት ቀን፡፡

وَلَا يَسْأَلُ حَمِيمٌ حَمِيمًا
( 10 ) 
ዘመድም ዘመድን በማይጠይቅበት ቀን፤ (መላሽ የለውም)፡፡

يُبَصَّرُونَهُمْ ۚ يَوَدُّ الْمُجْرِمُ لَوْ يَفْتَدِي مِنْ عَذَابِ يَوْمِئِذٍ بِبَنِيهِ
( 11 ) 
(ዘመዶቻቸውን) ያዩዋቸዋል፡፡ አመጸኛው ከዚያ ቀን ስቃይ (ነፍሱን) በልጆቹ ሊበዥ ይመኛል፡፡

وَصَاحِبَتِهِ وَأَخِيهِ
( 12 ) 
በሚስቱም በወንድሙም፡፡

وَفَصِيلَتِهِ الَّتِي تُؤْوِيهِ
( 13 ) 
በዚያችም በምታስጠጋው ጎሳው፡፡

وَمَن فِي الْأَرْضِ جَمِيعًا ثُمَّ يُنجِيهِ
( 14 ) 
በምድርም ላይ ባለው ሁሉ (ሊበዥ) ከዚያም ሊያድነው (ይመኛል)፡፡

كَلَّا ۖ إِنَّهَا لَظَىٰ
( 15 ) 
ይተው! እርሷ (እሳቲቱ) ለዟ ናት፡፡

نَزَّاعَةً لِّلشَّوَىٰ
( 16 ) 
የራስን ቅል ቆዳ የምትሞሽልቅ ስትኾን፡፡

تَدْعُو مَنْ أَدْبَرَ وَتَوَلَّىٰ
( 17 ) 
(ከእምነት) የዞረንና የሸሸን ሰው (ወደእርሷ) ትጠራለች፡፡

وَجَمَعَ فَأَوْعَىٰ
( 18 ) 
ገንዘብን የሰበሰበንና (ዘካውን ሳይሰጥ) የቆጠረንም፤ (ትጠራለች)፡፡

إِنَّ الْإِنسَانَ خُلِقَ هَلُوعًا
( 19 ) 
ሰው ቅጠ ቢስ ኾኖ ተፈጠረ፡፡

إِذَا مَسَّهُ الشَّرُّ جَزُوعًا
( 20 ) 
ክፉ ነገር ባገኘው ጊዜ ብስጪተኛ፡፡

وَإِذَا مَسَّهُ الْخَيْرُ مَنُوعًا
( 21 ) 
መልካምም ነገር (ድሎት) ባገኘ ጊዜ ከልካይ (ኾኖ ተፈጠረ)፡፡

إِلَّا الْمُصَلِّينَ
( 22 ) 
ሰጋጆቹ ብቻ ሲቀሩ፡፡

الَّذِينَ هُمْ عَلَىٰ صَلَاتِهِمْ دَائِمُونَ
( 23 ) 
እነዚያ እነርሱ በስግደታቸው ላይ ዘውታሪዎች የኾኑት፡፡

وَالَّذِينَ فِي أَمْوَالِهِمْ حَقٌّ مَّعْلُومٌ
( 24 ) 
እነዚያም በገንዘቦቻቸው ላይ የታወቀ መብት ያለባቸው የኾኑት፡፡

لِّلسَّائِلِ وَالْمَحْرُومِ
( 25 ) 
ለለማኝ ከልመና ለሚከለከልም (መብት ያለባቸው የኾኑት)፡፡

وَالَّذِينَ يُصَدِّقُونَ بِيَوْمِ الدِّينِ
( 26 ) 
እነዚያም በፍርዱ ቀን እውነት የሚሉት (የሚያረጋግጡት)፡፡

وَالَّذِينَ هُم مِّنْ عَذَابِ رَبِّهِم مُّشْفِقُونَ
( 27 ) 
እነዚያም እነርሱ ከጌታቸው ቅጣት ፈሪዎች የኾኑት፡፡

إِنَّ عَذَابَ رَبِّهِمْ غَيْرُ مَأْمُونٍ
( 28 ) 
የጌታቸው ቅጣት (መምጣቱ) የማያስተማምን ነውና፡፡

وَالَّذِينَ هُمْ لِفُرُوجِهِمْ حَافِظُونَ
( 29 ) 
እነዚያም እነርሱ ብልቶቻቸውን ጠባቂዎች የኾኑት፡፡

إِلَّا عَلَىٰ أَزْوَاجِهِمْ أَوْ مَا مَلَكَتْ أَيْمَانُهُمْ فَإِنَّهُمْ غَيْرُ مَلُومِينَ
( 30 ) 
በሚስቶቻቸው ወይም እጆቻቸው በያዙዋቸው (ባሪያዎች) ላይ ሲቀር፡፡ እነርሱ (በእነዚህ) የማይወቀሱ ናቸውና፡፡

فَمَنِ ابْتَغَىٰ وَرَاءَ ذَٰلِكَ فَأُولَٰئِكَ هُمُ الْعَادُونَ
( 31 ) 
ከዚያም ወዲያ የፈለገ ሰው እነዚያ እነሱ ድንበር አላፊዎች ናቸው፡፡

وَالَّذِينَ هُمْ لِأَمَانَاتِهِمْ وَعَهْدِهِمْ رَاعُونَ
( 32 ) 
እነዚያም እነርሱ አደራዎቻቸውንና ቃል ኪዳናቸውን ጠባቂዎች የኾኑት፡፡

وَالَّذِينَ هُم بِشَهَادَاتِهِمْ قَائِمُونَ
( 33 ) 
እነዚያም እነርሱ በምስክርነታቸው ትክክለኞች የኾኑት፡፡

وَالَّذِينَ هُمْ عَلَىٰ صَلَاتِهِمْ يُحَافِظُونَ
( 34 ) 
እነዚያም እነርሱ በሶላቶቻቸው ላይ የሚጠባበቁት፡፡

أُولَٰئِكَ فِي جَنَّاتٍ مُّكْرَمُونَ
( 35 ) 
እነዚህ (ከዚህ በላይ የተወሱት ሁሉ) በገነቶች ውስጥ የሚከበሩ ናቸው፡፡

فَمَالِ الَّذِينَ كَفَرُوا قِبَلَكَ مُهْطِعِينَ
( 36 ) 
ለእነዚያም ለካዱት ወደ አንተ በኩል አንገቶቻቸውን መዝዘው የሚያተኩሩት ምን አላቸው?

عَنِ الْيَمِينِ وَعَنِ الشِّمَالِ عِزِينَ
( 37 ) 
ከቀኝና ከግራ ክፍልፍል ጭፍሮች ሲኾኑ፡፡

أَيَطْمَعُ كُلُّ امْرِئٍ مِّنْهُمْ أَن يُدْخَلَ جَنَّةَ نَعِيمٍ
( 38 ) 
ከእነርሱ እያንዳንዱ ሰው የጸጋይቱን ገነት መግባትን ይከጅላልን?

كَلَّا ۖ إِنَّا خَلَقْنَاهُم مِّمَّا يَعْلَمُونَ
( 39 ) 
ይከልከል፤ እኛ ከሚያውቁት ነገር (ከፍቶት ጠብታ) ፈጠርናቸው፡፡

فَلَا أُقْسِمُ بِرَبِّ الْمَشَارِقِ وَالْمَغَارِبِ إِنَّا لَقَادِرُونَ
( 40 ) 
በምሥራቆችና በምዕራቦችም ጌታ እምላለሁ፡፡ እኛ በእርግጥ ቻዮች ነን፡፡

عَلَىٰ أَن نُّبَدِّلَ خَيْرًا مِّنْهُمْ وَمَا نَحْنُ بِمَسْبُوقِينَ
( 41 ) 
ከእነርሱ የተሻለን በመለወጥ ላይ፡፡ እኛም ተሸናፊዎች አይደለንም፡፡

فَذَرْهُمْ يَخُوضُوا وَيَلْعَبُوا حَتَّىٰ يُلَاقُوا يَوْمَهُمُ الَّذِي يُوعَدُونَ
( 42 ) 
ያንንም የሚስፈራሩበትን ቀናቸውን እስከሚገናኙ ድረስ ተዋቸው፡፡ ይዋኙ ይጫወቱም፡፡

يَوْمَ يَخْرُجُونَ مِنَ الْأَجْدَاثِ سِرَاعًا كَأَنَّهُمْ إِلَىٰ نُصُبٍ يُوفِضُونَ
( 43 ) 
ወደ ጣዖቶች እንደሚሽቀዳደሙ ኾነው ከመቃብሮቻቸው ፈጥነው የሚወጡበትን ቀን (እስከሚገናኙ ድረስ ተዋቸው)፡፡

خَاشِعَةً أَبْصَارُهُمْ تَرْهَقُهُمْ ذِلَّةٌ ۚ ذَٰلِكَ الْيَوْمُ الَّذِي كَانُوا يُوعَدُونَ
( 44 ) 
ዓይኖቻቸው ያፈሩ ኾነው ውርደት ትሸፍናቸዋለች፡፡ ይህ ቀን ያ ይስፈራሩበት የነበሩት ነው፡፡
