አማርኛ Muhammad Sadiq & Sani Habib
Surah አል ነበእ - Aya count 40
عَمَّ يَتَسَاءَلُونَ
( 1 ) 
ከምን ነገር ይጠያየቃሉ?

عَنِ النَّبَإِ الْعَظِيمِ
( 2 ) 
ከታላቁ ዜና (ከቁርኣን ይጠያየቃሉ)፡፡

الَّذِي هُمْ فِيهِ مُخْتَلِفُونَ
( 3 ) 
ከዚያ እነርሱ በእርሱ የተለያዩበት ከኾነው፡፡

كَلَّا سَيَعْلَمُونَ
( 4 ) 
ይከልከሉ፤ ወደፊት (የሚደርስበቸውን) በእርግጥ ያውቃሉ፡፡

ثُمَّ كَلَّا سَيَعْلَمُونَ
( 5 ) 
ከዚያም ይከልከሉ፤ ወደፊት ያውቃሉ፡፡

أَلَمْ نَجْعَلِ الْأَرْضَ مِهَادًا
( 6 ) 
ምድርን ምንጣፍ አላደረግንምን?

وَالْجِبَالَ أَوْتَادًا
( 7 ) 
ጋራዎችንም ችካሎች አላደረግንምን?

وَخَلَقْنَاكُمْ أَزْوَاجًا
( 8 ) 
ብዙ ዓይነቶችም አድርገን ፈጠርናችሁ፡፡

وَجَعَلْنَا نَوْمَكُمْ سُبَاتًا
( 9 ) 
እንቅልፋችሁንም ዕረፍት አደረግን፡፡

وَجَعَلْنَا اللَّيْلَ لِبَاسًا
( 10 ) 
ሌሊቱንም ልባስ አደረግን፡፡

وَجَعَلْنَا النَّهَارَ مَعَاشًا
( 11 ) 
ቀኑንም (ለኑሮ) መስሪያ አደረግን፡፡

وَبَنَيْنَا فَوْقَكُمْ سَبْعًا شِدَادًا
( 12 ) 
ከበላያችሁም ሰባትን ብርቱዎች (ሰማያት) ገነባን፡፡

وَجَعَلْنَا سِرَاجًا وَهَّاجًا
( 13 ) 
አንጸባራቂ ብርሃንንም አደረግን፡፡

وَأَنزَلْنَا مِنَ الْمُعْصِرَاتِ مَاءً ثَجَّاجًا
( 14 ) 
ከአረገዙት ደመናዎችም ተንቧቢ ውሃን አወረድን፡፡

لِّنُخْرِجَ بِهِ حَبًّا وَنَبَاتًا
( 15 ) 
በእርሱ እኽልንና ቅጠላ ቅጠልን እናወጣ ዘንድ (አወረድን)፡፡

وَجَنَّاتٍ أَلْفَافًا
( 16 ) 
የተቆላለፉ አትክልቶችንም፡፡

إِنَّ يَوْمَ الْفَصْلِ كَانَ مِيقَاتًا
( 17 ) 
የመለያው ቀን የተወሰነ ጊዜ ነው፡፡

يَوْمَ يُنفَخُ فِي الصُّورِ فَتَأْتُونَ أَفْوَاجًا
( 18 ) 
በቀንዱ በሚነፋና የተለያዩ ጭፍሮች ኾናችሁ በምትመጡ ቀን ነው፡፡

وَفُتِحَتِ السَّمَاءُ فَكَانَتْ أَبْوَابًا
( 19 ) 
ሰማይም በምትከፈትና (ባለ) ደጃፎችም በምትኾንበት፡፡

وَسُيِّرَتِ الْجِبَالُ فَكَانَتْ سَرَابًا
( 20 ) 
ጋራዎችም በሚነዱበት (እንደ) ሲሪብዱም በሚኾኑበት (ቀን) ነው፡፡

إِنَّ جَهَنَّمَ كَانَتْ مِرْصَادًا
( 21 ) 
ገሀነም መጠባበቂያ (ስፍራ) ናት፡፡

لِّلطَّاغِينَ مَآبًا
( 22 ) 
ለሕግ ተላላፊዎች መመለሻ ስትኾን፡፡

لَّابِثِينَ فِيهَا أَحْقَابًا
( 23 ) 
በውስጧ ብዙን ዘመናት ነዋሪዎች ሲኾኑ፤

لَّا يَذُوقُونَ فِيهَا بَرْدًا وَلَا شَرَابًا
( 24 ) 
በውስጧ ቅዝቃዜንም መጠጥንም አይቀምሱም፡፡

إِلَّا حَمِيمًا وَغَسَّاقًا
( 25 ) 
ግን ሙቅ ውሃንና እዥን (ይቀምሳሉ)፡፡

جَزَاءً وِفَاقًا
( 26 ) 
ተስማሚን ምንዳ ይምመነዳሉ፡፡

إِنَّهُمْ كَانُوا لَا يَرْجُونَ حِسَابًا
( 27 ) 
እነርሱ ምርመራን የማይፈሩ ነበሩና፡፡

وَكَذَّبُوا بِآيَاتِنَا كِذَّابًا
( 28 ) 
በአንቀጾቻችንም ማስተባበልን አስተባበሉና፡፡

وَكُلَّ شَيْءٍ أَحْصَيْنَاهُ كِتَابًا
( 29 ) 
ነገሩንም ሁሉ የተጻፈ ሲኾን አጠቃለልነው፡፡

فَذُوقُوا فَلَن نَّزِيدَكُمْ إِلَّا عَذَابًا
( 30 ) 
ቅመሱም ቅጣትንም እንጅ (ሌላን) አንጨምራችሁም (ይባላሉ)፡፡

إِنَّ لِلْمُتَّقِينَ مَفَازًا
( 31 ) 
ለጥንቁቆቹ መዳኛ ስፍራ አልላቸው፡፡

حَدَائِقَ وَأَعْنَابًا
( 32 ) 
አትክልቶችና ወይኖችም፡፡

وَكَوَاعِبَ أَتْرَابًا
( 33 ) 
እኩያዎች የኾኑ ጡተ ጉቻማዎችም፡፡

وَكَأْسًا دِهَاقًا
( 34 ) 
የተሞሉ ብርጭቆዎችም፡፡

لَّا يَسْمَعُونَ فِيهَا لَغْوًا وَلَا كِذَّابًا
( 35 ) 
በውስጧ ትርፍ ቃልንም ማስዋሸትንም አይሰሙም፡፡

جَزَاءً مِّن رَّبِّكَ عَطَاءً حِسَابًا
( 36 ) 
ከጌታህ የኾነን ምንዳ በቂ ስጦታን (ተሰጡ)፡፡

رَّبِّ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ وَمَا بَيْنَهُمَا الرَّحْمَٰنِ ۖ لَا يَمْلِكُونَ مِنْهُ خِطَابًا
( 37 ) 
የሰማያትና የምድር በመካከላቸውም ያለው ሁሉ ጌታ በጣም አዛኝ ከኾነው (ተመነዱ)፡፡ ከእርሱ ጋር መነጋገርን አይችሉም፡፡

يَوْمَ يَقُومُ الرُّوحُ وَالْمَلَائِكَةُ صَفًّا ۖ لَّا يَتَكَلَّمُونَ إِلَّا مَنْ أَذِنَ لَهُ الرَّحْمَٰنُ وَقَالَ صَوَابًا
( 38 ) 
መንፈሱ (ጂብሪል) መላእክቶቹም የተሰለፉ ኾነው በሚቆሙ ቀን አል-ረሕማን ለእርሱ የፈቀደለትና ትክክለኛን ቃል ያለ ሰው ቢኾን እንጅ (መነጋገርን አይችሉም)፡፡

ذَٰلِكَ الْيَوْمُ الْحَقُّ ۖ فَمَن شَاءَ اتَّخَذَ إِلَىٰ رَبِّهِ مَآبًا
( 39 ) 
ይህ የተረጋገጠው ቀን ነው፡፡ የሻም ሰው ወደ ጌታው መመለስን ይይዛል፡፡

إِنَّا أَنذَرْنَاكُمْ عَذَابًا قَرِيبًا يَوْمَ يَنظُرُ الْمَرْءُ مَا قَدَّمَتْ يَدَاهُ وَيَقُولُ الْكَافِرُ يَا لَيْتَنِي كُنتُ تُرَابًا
( 40 ) 
እኛ ሰው ሁሉ እጆቹ ያስቀደሙትን በሚያይበትና ከሓዲውም ዋ ምኞቴ! ምንነው ዐፈር በኾንኩ በሚልበት ቀን ቅርብ የኾነን ቅጣት አስጠነቀቅናችሁ፡፡
