አማርኛ Muhammad Sadiq & Sani Habib
Surah አል ሓቃህ - Aya count 52
الْحَاقَّةُ
( 1 ) 
እውነትን አረጋጋጪቱ (ትንሣኤ)፡፡

مَا الْحَاقَّةُ
( 2 ) 
አረጋጋጪቱም (እርሷ) ምንድን ናት!

وَمَا أَدْرَاكَ مَا الْحَاقَّةُ
( 3 ) 
አረጋጋጪቱም ምን እንደኾነች ምን አሳወቀህ?

كَذَّبَتْ ثَمُودُ وَعَادٌ بِالْقَارِعَةِ
( 4 ) 
ሰሙድና ዓድ በቆርቋሪይቱ (ትንሣኤ) አስተባበሉ፡፡

فَأَمَّا ثَمُودُ فَأُهْلِكُوا بِالطَّاغِيَةِ
( 5 ) 
ሠሙድማ ወሰን በሌላት ጩኸት ተጠፋ፤ (ተወደሙ)፡፡

وَأَمَّا عَادٌ فَأُهْلِكُوا بِرِيحٍ صَرْصَرٍ عَاتِيَةٍ
( 6 ) 
ዓድማ በኀይል በምትንሻሻ ብርቱ ነፋስ ተጠፉ፡፡

سَخَّرَهَا عَلَيْهِمْ سَبْعَ لَيَالٍ وَثَمَانِيَةَ أَيَّامٍ حُسُومًا فَتَرَى الْقَوْمَ فِيهَا صَرْعَىٰ كَأَنَّهُمْ أَعْجَازُ نَخْلٍ خَاوِيَةٍ
( 7 ) 
ተከታታይ በኾኑ ሰባት ሌሊቶችና ስምንት መዓልቶች ውስጥ በእነርሱ ላይ ለቀቃት፡፡ ሕዝቦቹንም፤ በውስጧ የተጣሉ ኾነው ልክ ክፍት የኾኑ የዘንባባ ግንዶች መስለው ታያቸዋለህ፡፡

فَهَلْ تَرَىٰ لَهُم مِّن بَاقِيَةٍ
( 8 ) 
ለእነርሱም ቀሪን ታያለህን?

وَجَاءَ فِرْعَوْنُ وَمَن قَبْلَهُ وَالْمُؤْتَفِكَاتُ بِالْخَاطِئَةِ
( 9 ) 
ፈርዖን ከበፊቱ የነበሩትም ሰዎች ተገልባጮቹም (ከተሞች) በኀጢአት (ሥራዎች) መጡ፡፡

فَعَصَوْا رَسُولَ رَبِّهِمْ فَأَخَذَهُمْ أَخْذَةً رَّابِيَةً
( 10 ) 
የጌታቸውንም መልእክተኛ ትዕዛዝ ጣሱ፡፡ የበረታችንም አያያዝ ያዛቸው፡፡

إِنَّا لَمَّا طَغَى الْمَاءُ حَمَلْنَاكُمْ فِي الْجَارِيَةِ
( 11 ) 
እኛ ውሃው ባየለ ጊዜ በተንሻላይቱ ታንኳ ውስጥ ጫንናችሁ፡፡

لِنَجْعَلَهَا لَكُمْ تَذْكِرَةً وَتَعِيَهَا أُذُنٌ وَاعِيَةٌ
( 12 ) 
ለእናንተ መገሰጫ ልናደርጋት አጥኒ የኾነችም ጆሮ ታጠናት ዘንድ፡፡

فَإِذَا نُفِخَ فِي الصُّورِ نَفْخَةٌ وَاحِدَةٌ
( 13 ) 
በቀንዱም አንዲት መንነፋት በተነፋች ጊዜ፡፡

وَحُمِلَتِ الْأَرْضُ وَالْجِبَالُ فَدُكَّتَا دَكَّةً وَاحِدَةً
( 14 ) 
ምድርና ጋራዎችም (ከስፍራቸው) በተነሱና አንዲትን መሰባበር በተሰባበሩ ጊዜ፡፡

فَيَوْمَئِذٍ وَقَعَتِ الْوَاقِعَةُ
( 15 ) 
በዚያ ቀን ኋኝቱ (ትንሣኤ) ትኾናለች፡፡

وَانشَقَّتِ السَّمَاءُ فَهِيَ يَوْمَئِذٍ وَاهِيَةٌ
( 16 ) 
ሰማይም ትቀደዳለች፡፡ ስለዚህ እርሷ በዚያ ቀን ደካማ ናት፡፡

وَالْمَلَكُ عَلَىٰ أَرْجَائِهَا ۚ وَيَحْمِلُ عَرْشَ رَبِّكَ فَوْقَهُمْ يَوْمَئِذٍ ثَمَانِيَةٌ
( 17 ) 
መላእክትም በየጫፎችዋ ላይ ይኾናሉ፡፡ የጌታህንም ዐርሽ በዚያ ቀን ስምንት መላእክት ከበላያቸው ይሸከማሉ፡፡

يَوْمَئِذٍ تُعْرَضُونَ لَا تَخْفَىٰ مِنكُمْ خَافِيَةٌ
( 18 ) 
በዚያ ቀን ከእናንተ ተደባቂ (ነገሮች) የማይደበቁ ሲኾኑ ትቅቀረባላችሁ፡፡

فَأَمَّا مَنْ أُوتِيَ كِتَابَهُ بِيَمِينِهِ فَيَقُولُ هَاؤُمُ اقْرَءُوا كِتَابِيَهْ
( 19 ) 
መጽሐፉን በቀኙ የተሰጠ ሰውማ (ለጓደኞቹ) «እንኩ፤ መጽሐፌን አንብቡ» ይላል፡፡

إِنِّي ظَنَنتُ أَنِّي مُلَاقٍ حِسَابِيَهْ
( 20 ) 
«እኔ ምርመራየን የምገናኝ መኾኔን አረጋገጥኩ፤» (ተዘጋጀሁም ይላል)፡፡

فَهُوَ فِي عِيشَةٍ رَّاضِيَةٍ
( 21 ) 
እርሱም በተወደደች ኑሮ ውሰጥ ይኾናል፡፡

فِي جَنَّةٍ عَالِيَةٍ
( 22 ) 
በከፍተኛይቱ ገነት ውስጥ፡፡

قُطُوفُهَا دَانِيَةٌ
( 23 ) 
ፍሬዎችዋ ቅርቦች የኾኑ፡፡

كُلُوا وَاشْرَبُوا هَنِيئًا بِمَا أَسْلَفْتُمْ فِي الْأَيَّامِ الْخَالِيَةِ
( 24 ) 
በአለፉት ቀናት ውስጥ (በምድረ ዓለም) ባስቀደማችሁት ምክንያት ብሉ፤ ጠጡም፤ (ይባላሉ)፡፡

وَأَمَّا مَنْ أُوتِيَ كِتَابَهُ بِشِمَالِهِ فَيَقُولُ يَا لَيْتَنِي لَمْ أُوتَ كِتَابِيَهْ
( 25 ) 
መጽሐፉንም በግራው የተሰጠማ «ዋ ጥፋቴ! ምነው መጽሐፌን ባልተሰጠሁ» ይላል፡፡

وَلَمْ أَدْرِ مَا حِسَابِيَهْ
( 26 ) 
«ምርመራየንም ምን እንደኾነ ባላወቅኩ፡፡

يَا لَيْتَهَا كَانَتِ الْقَاضِيَةَ
( 27 ) 
«እርሷ (ሞት ሕይወቴን) ምነው ፈጻሚ በኾነች፡፡

مَا أَغْنَىٰ عَنِّي مَالِيَهْ ۜ
( 28 ) 
«ገንዘቤ ከእኔ ምንንም አላብቃቃኝ፤ (አልጠቀመኝም)፡፡

هَلَكَ عَنِّي سُلْطَانِيَهْ
( 29 ) 
«ኀይሌ ከእኔ ላይ ጠፋ» (ይላል)፡፡

خُذُوهُ فَغُلُّوهُ
( 30 ) 
«ያዙት፤ እሰሩትም፡፡

ثُمَّ الْجَحِيمَ صَلُّوهُ
( 31 ) 
«ከዚያም በእሳት ውሰጥ አግቡት፡፡

ثُمَّ فِي سِلْسِلَةٍ ذَرْعُهَا سَبْعُونَ ذِرَاعًا فَاسْلُكُوهُ
( 32 ) 
«ከዚያም ርዝመቷ ሰባ ክንድ በኾነች ሰንሰለት ውስጥ አግቡት፡፡»

إِنَّهُ كَانَ لَا يُؤْمِنُ بِاللَّهِ الْعَظِيمِ
( 33 ) 
እርሱ ታላቅ በኾነው አላህ አያምንም ነበርና፡፡

وَلَا يَحُضُّ عَلَىٰ طَعَامِ الْمِسْكِينِ
( 34 ) 
ድኾችንም በማብላት ላይ አያግባባም ነበርና፡፡

فَلَيْسَ لَهُ الْيَوْمَ هَاهُنَا حَمِيمٌ
( 35 ) 
ለእርሱም ዛሬ እዚህ ዘመድ የለውም፡፡

وَلَا طَعَامٌ إِلَّا مِنْ غِسْلِينٍ
( 36 ) 
ምግብም ከእሳት ሰዎች ቁስል እጣቢ (እዥ) በስተቀር የለውም፡፡

لَّا يَأْكُلُهُ إِلَّا الْخَاطِئُونَ
( 37 ) 
ኀጢኣተኞች እንጅ ሌላ አይበላውም፤ (ይባላል)፡፡

فَلَا أُقْسِمُ بِمَا تُبْصِرُونَ
( 38 ) 
በምታዩትም ነገር እምላለሁ፡፡

وَمَا لَا تُبْصِرُونَ
( 39 ) 
በማታዩትም ነገር፡፡

إِنَّهُ لَقَوْلُ رَسُولٍ كَرِيمٍ
( 40 ) 
እርሱ (ቁርኣን) የተከበረ መልክተኛ ቃል ነው፡፡

وَمَا هُوَ بِقَوْلِ شَاعِرٍ ۚ قَلِيلًا مَّا تُؤْمِنُونَ
( 41 ) 
እርሱም የባለቅኔ ቃል (ግጥም) አይደለም፡፡ ጥቂትን ብቻ ታምናላችሁ፡፡

وَلَا بِقَوْلِ كَاهِنٍ ۚ قَلِيلًا مَّا تَذَكَّرُونَ
( 42 ) 
የጠንቋይም ቃል አይደለም፡፡ ጥቂትን ብቻ ታስታውሳላችሁ፡፡

تَنزِيلٌ مِّن رَّبِّ الْعَالَمِينَ
( 43 ) 
ከዓለማት ጌታ የተወረደ ነው፡፡

وَلَوْ تَقَوَّلَ عَلَيْنَا بَعْضَ الْأَقَاوِيلِ
( 44 ) 
በእኛ ላይም ከፊልን ቃላት (ያላልነውን) በቀጠፈ ኖሮ፤

لَأَخَذْنَا مِنْهُ بِالْيَمِينِ
( 45 ) 
በኀይል በያዝነው ነበር፡፡

ثُمَّ لَقَطَعْنَا مِنْهُ الْوَتِينَ
( 46 ) 
ከዚያም ከእርሱ የልቡን ሥር (የተንጠለጠለበትን ጅማት) በቆረጥን ነበር፡፡

فَمَا مِنكُم مِّنْ أَحَدٍ عَنْهُ حَاجِزِينَ
( 47 ) 
ከእናንተም ውስጥ ከእርሱ ላይ ከልካዮች ምንም አይኖሩም፡፡

وَإِنَّهُ لَتَذْكِرَةٌ لِّلْمُتَّقِينَ
( 48 ) 
እርሱም (ቁርኣን) ለጥንቁቆቹ መገሠጫ ነው፡፡

وَإِنَّا لَنَعْلَمُ أَنَّ مِنكُم مُّكَذِّبِينَ
( 49 ) 
እኛም ከእናንተ ውስጥ አስተባባዮች መኖራቸውን በእርግጥ እናውቃለን፡፡

وَإِنَّهُ لَحَسْرَةٌ عَلَى الْكَافِرِينَ
( 50 ) 
እርሱም (ቁርኣን) በከሓዲዎቹ ላይ ጸጸት ነው፡፡

وَإِنَّهُ لَحَقُّ الْيَقِينِ
( 51 ) 
እርሱም የተረጋገጠ እውነት ነው፡፡

فَسَبِّحْ بِاسْمِ رَبِّكَ الْعَظِيمِ
( 52 ) 
የታላቁን ጌታህንም ስም አወድስ፡፡
