Surah አል ናዚዓት

አማርኛ Muhammad Sadiq & Sani Habib

Surah አል ናዚዓት - Aya count 46
Facebook Twitter Google+ Pinterest Reddit StumbleUpon Linkedin Tumblr Google Bookmarks Email
وَالنَّازِعَاتِ غَرْقًا ( 1 ) አል ናዚዓት - Aya 1
በኃይል አውጪዎች በኾኑት፤ አል ናዚዓት - Aya 1
وَالنَّاشِطَاتِ نَشْطًا ( 2 ) አል ናዚዓት - Aya 2
በቀስታ መምዘዝንም መዘዦች በኾኑት፤ አል ናዚዓት - Aya 2
وَالسَّابِحَاتِ سَبْحًا ( 3 ) አል ናዚዓት - Aya 3
መዋኘትም ዋኚዎች በኾኑት፤ አል ናዚዓት - Aya 3
فَالسَّابِقَاتِ سَبْقًا ( 4 ) አል ናዚዓት - Aya 4
መቅደምንም ቀዳሚዎች በኾኑት፤ አል ናዚዓት - Aya 4
فَالْمُدَبِّرَاتِ أَمْرًا ( 5 ) አል ናዚዓት - Aya 5
ነገርንም አስተናባሪዎች በኾኑት (መላእክት) እምላለሁ፡፡ (በእርግጥ ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡ አል ናዚዓት - Aya 5
يَوْمَ تَرْجُفُ الرَّاجِفَةُ ( 6 ) አል ናዚዓት - Aya 6
ተርገፍጋፊይቱ (ምድር) በምትርገፈገፍበት ቀን፤ አል ናዚዓት - Aya 6
تَتْبَعُهَا الرَّادِفَةُ ( 7 ) አል ናዚዓት - Aya 7
ለጣቂይቱ የምትከተላት ስትኾን (ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡ አል ናዚዓት - Aya 7
قُلُوبٌ يَوْمَئِذٍ وَاجِفَةٌ ( 8 ) አል ናዚዓት - Aya 8
በዚያ ቀን ልቦች ተሸባሪዎች ናቸው፡፡ አል ናዚዓት - Aya 8
أَبْصَارُهَا خَاشِعَةٌ ( 9 ) አል ናዚዓት - Aya 9
ዓይኖቻቸው ተዋራጆች (አቀርቃሪዎች) ናቸው፡፡ አል ናዚዓት - Aya 9
يَقُولُونَ أَإِنَّا لَمَرْدُودُونَ فِي الْحَافِرَةِ ( 10 ) አል ናዚዓት - Aya 10
«እኛ ወደ መጀመሪያይቱ ኹነታ ተመላሾች ነን?» ይላሉ፡፡ አል ናዚዓት - Aya 10
أَإِذَا كُنَّا عِظَامًا نَّخِرَةً ( 11 ) አል ናዚዓት - Aya 11
«የበሰበሱ አጥንቶች በኾን ጊዜ (እንቀሰቀሳለን?)» አል ናዚዓት - Aya 11
قَالُوا تِلْكَ إِذًا كَرَّةٌ خَاسِرَةٌ ( 12 ) አል ናዚዓት - Aya 12
«ይህቺ ያን ጊዜ ባለ ከሳራ መመለስ ናት» ይላሉ፡፡ አል ናዚዓት - Aya 12
فَإِنَّمَا هِيَ زَجْرَةٌ وَاحِدَةٌ ( 13 ) አል ናዚዓት - Aya 13
እርሷም አንዲት ጩኸት ብቻ ናት፡፡ አል ናዚዓት - Aya 13
فَإِذَا هُم بِالسَّاهِرَةِ ( 14 ) አል ናዚዓት - Aya 14
ወዲያውኑም እነርሱ እንቅልፍ በሌለባት (ምድር) ላይ ይኾናሉ፡፡ አል ናዚዓት - Aya 14
هَلْ أَتَاكَ حَدِيثُ مُوسَىٰ ( 15 ) አል ናዚዓት - Aya 15
የሙሳ ወሬ መጣልህን? አል ናዚዓት - Aya 15
إِذْ نَادَاهُ رَبُّهُ بِالْوَادِ الْمُقَدَّسِ طُوًى ( 16 ) አል ናዚዓት - Aya 16
ጌታው በተቀደሰው ሸለቆ በጡዋ በጠራው ጊዜ፤ አል ናዚዓት - Aya 16
اذْهَبْ إِلَىٰ فِرْعَوْنَ إِنَّهُ طَغَىٰ ( 17 ) አል ናዚዓት - Aya 17
ወደ ፈርዖን ኺድ፡፡ እርሱ ወሰን አልፏልና፡፡ አል ናዚዓት - Aya 17
فَقُلْ هَل لَّكَ إِلَىٰ أَن تَزَكَّىٰ ( 18 ) አል ናዚዓት - Aya 18
በለውም፡- «ወደ መጥራራትህ ላንተ (መንገድ) አለህን?» አል ናዚዓት - Aya 18
وَأَهْدِيَكَ إِلَىٰ رَبِّكَ فَتَخْشَىٰ ( 19 ) አል ናዚዓት - Aya 19
«ወደ ጌታህም ልመራህ ትፈራውም ዘንድ፤ (መንገድ አለህን?)» አለው፡፡ አል ናዚዓት - Aya 19
فَأَرَاهُ الْآيَةَ الْكُبْرَىٰ ( 20 ) አል ናዚዓት - Aya 20
ታላቂቱንም ተዓምር አሳየው፡፡ አል ናዚዓት - Aya 20
فَكَذَّبَ وَعَصَىٰ ( 21 ) አል ናዚዓት - Aya 21
አስተባበለም፤ አመጸም፡፡ አል ናዚዓት - Aya 21
ثُمَّ أَدْبَرَ يَسْعَىٰ ( 22 ) አል ናዚዓት - Aya 22
ከዚያም (ለማጥፋት) የሚተጋ ኾኖ ዞረ፡፡ አል ናዚዓት - Aya 22
فَحَشَرَ فَنَادَىٰ ( 23 ) አል ናዚዓት - Aya 23
(ሰራዊቶቹን) ሰበሰበም፤ ተጣራም፡፡ አል ናዚዓት - Aya 23
فَقَالَ أَنَا رَبُّكُمُ الْأَعْلَىٰ ( 24 ) አል ናዚዓት - Aya 24
አለም፡- «እኔ ታላቁ ጌታችሁ ነኝ፡፡» አል ናዚዓት - Aya 24
فَأَخَذَهُ اللَّهُ نَكَالَ الْآخِرَةِ وَالْأُولَىٰ ( 25 ) አል ናዚዓት - Aya 25
አላህም በኋለኛይቱና በፊተኛይቱ (ቃል) ቅጣት ያዘው፡፡ አል ናዚዓት - Aya 25
إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَعِبْرَةً لِّمَن يَخْشَىٰ ( 26 ) አል ናዚዓት - Aya 26
በዚህ ውስጥ ለሚፈራ ሰው በእርግጥ መገምገሚያ አለበት፡፡ አል ናዚዓት - Aya 26
أَأَنتُمْ أَشَدُّ خَلْقًا أَمِ السَّمَاءُ ۚ بَنَاهَا ( 27 ) አል ናዚዓት - Aya 27
ባፈጣጠር እናንተ ይበልጥ የበረታችሁ ናችሁን? ወይንስ ሰማይ? (አላህ) ገነባት፡፡ አል ናዚዓት - Aya 27
رَفَعَ سَمْكَهَا فَسَوَّاهَا ( 28 ) አል ናዚዓት - Aya 28
ከፍታዋን አጓነ፤ አስተካከላትም፡፡ አል ናዚዓት - Aya 28
وَأَغْطَشَ لَيْلَهَا وَأَخْرَجَ ضُحَاهَا ( 29 ) አል ናዚዓት - Aya 29
ሌሊቷንም አጨለመ፡፡ ቀንዋንም ገለጸ፡፡ አል ናዚዓት - Aya 29
وَالْأَرْضَ بَعْدَ ذَٰلِكَ دَحَاهَا ( 30 ) አል ናዚዓት - Aya 30
ምድርንም ከዚህ በኋላ ዘረጋት፡፡ አል ናዚዓት - Aya 30
أَخْرَجَ مِنْهَا مَاءَهَا وَمَرْعَاهَا ( 31 ) አል ናዚዓት - Aya 31
ውሃዋንና ግጦሿን ከእርሷ አወጣ፡፡ አል ናዚዓት - Aya 31
وَالْجِبَالَ أَرْسَاهَا ( 32 ) አል ናዚዓት - Aya 32
ጋራዎችንም አደላደላቸው፡፡ አል ናዚዓት - Aya 32
مَتَاعًا لَّكُمْ وَلِأَنْعَامِكُمْ ( 33 ) አል ናዚዓት - Aya 33
ለእናንተና ለእንስሶቻችሁ መጣቀሚያ ይኾን ዘንድ (ይህን አደረገ)፡፡ አል ናዚዓት - Aya 33
فَإِذَا جَاءَتِ الطَّامَّةُ الْكُبْرَىٰ ( 34 ) አል ናዚዓት - Aya 34
ታላቂቱም መዐት በመጣች ጊዜ፣ አል ናዚዓት - Aya 34
يَوْمَ يَتَذَكَّرُ الْإِنسَانُ مَا سَعَىٰ ( 35 ) አል ናዚዓት - Aya 35
ሰው ሁሉ የሠራውን በሚያስታውስበት ቀን፣ አል ናዚዓት - Aya 35
وَبُرِّزَتِ الْجَحِيمُ لِمَن يَرَىٰ ( 36 ) አል ናዚዓት - Aya 36
ገሀነምም ለሚያይ ሰው በተገለጠች ጊዜ፣ አል ናዚዓት - Aya 36
فَأَمَّا مَن طَغَىٰ ( 37 ) አል ናዚዓት - Aya 37
የካደ ሰውማ፣ አል ናዚዓት - Aya 37
وَآثَرَ الْحَيَاةَ الدُّنْيَا ( 38 ) አል ናዚዓት - Aya 38
ቅርቢቱንም ሕይወት የመረጠ፣ አል ናዚዓት - Aya 38
فَإِنَّ الْجَحِيمَ هِيَ الْمَأْوَىٰ ( 39 ) አል ናዚዓት - Aya 39
ገሀነም እርሷ በእርግጥ መኖሪያው ናት፡፡ አል ናዚዓት - Aya 39
وَأَمَّا مَنْ خَافَ مَقَامَ رَبِّهِ وَنَهَى النَّفْسَ عَنِ الْهَوَىٰ ( 40 ) አል ናዚዓት - Aya 40
በጌታው ፊት መቆምን የፈራ ሰውማ ነፍሱንም ከዝንባሌዋ የከለከለ አል ናዚዓት - Aya 40
فَإِنَّ الْجَنَّةَ هِيَ الْمَأْوَىٰ ( 41 ) አል ናዚዓት - Aya 41
ገነት እርሷ በእርግጥ መኖሪያው ናት፡፡ አል ናዚዓት - Aya 41
يَسْأَلُونَكَ عَنِ السَّاعَةِ أَيَّانَ مُرْسَاهَا ( 42 ) አል ናዚዓት - Aya 42
«ከሰዓቲቱ መቼ ነው መኾኛዋ?» ሲሉ ይጠይቁሃል፡፡ አል ናዚዓት - Aya 42
فِيمَ أَنتَ مِن ذِكْرَاهَا ( 43 ) አል ናዚዓት - Aya 43
አንተ እርሷን ከማስታወስ በምን ውስጥ ነህ? አል ናዚዓት - Aya 43
إِلَىٰ رَبِّكَ مُنتَهَاهَا ( 44 ) አል ናዚዓት - Aya 44
(የዕውቀት) መጨረሻዋ ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡ አል ናዚዓት - Aya 44
إِنَّمَا أَنتَ مُنذِرُ مَن يَخْشَاهَا ( 45 ) አል ናዚዓት - Aya 45
አንተ የሚፈራትን ሰው አስፈራሪ ብቻ ነህ፡፡ አል ናዚዓት - Aya 45
كَأَنَّهُمْ يَوْمَ يَرَوْنَهَا لَمْ يَلْبَثُوا إِلَّا عَشِيَّةً أَوْ ضُحَاهَا ( 46 ) አል ናዚዓት - Aya 46
እነርሱ በሚያዩዋት ቀን ያንዲት ቀን ምሽትን ወይም ረፏዷን እንጅ ያልቆዩ ይመስላሉ፡፡ አል ናዚዓት - Aya 46
Facebook Twitter Google+ Pinterest Reddit StumbleUpon Linkedin Tumblr Google Bookmarks Email

Select Translation

Select surah