አማርኛ Muhammad Sadiq & Sani Habib
Surah አል ናዚዓት - Aya count 46
وَالنَّازِعَاتِ غَرْقًا
( 1 ) 
በኃይል አውጪዎች በኾኑት፤

وَالنَّاشِطَاتِ نَشْطًا
( 2 ) 
በቀስታ መምዘዝንም መዘዦች በኾኑት፤

وَالسَّابِحَاتِ سَبْحًا
( 3 ) 
መዋኘትም ዋኚዎች በኾኑት፤

فَالسَّابِقَاتِ سَبْقًا
( 4 ) 
መቅደምንም ቀዳሚዎች በኾኑት፤

فَالْمُدَبِّرَاتِ أَمْرًا
( 5 ) 
ነገርንም አስተናባሪዎች በኾኑት (መላእክት) እምላለሁ፡፡ (በእርግጥ ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡

يَوْمَ تَرْجُفُ الرَّاجِفَةُ
( 6 ) 
ተርገፍጋፊይቱ (ምድር) በምትርገፈገፍበት ቀን፤

تَتْبَعُهَا الرَّادِفَةُ
( 7 ) 
ለጣቂይቱ የምትከተላት ስትኾን (ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡

قُلُوبٌ يَوْمَئِذٍ وَاجِفَةٌ
( 8 ) 
በዚያ ቀን ልቦች ተሸባሪዎች ናቸው፡፡

أَبْصَارُهَا خَاشِعَةٌ
( 9 ) 
ዓይኖቻቸው ተዋራጆች (አቀርቃሪዎች) ናቸው፡፡

يَقُولُونَ أَإِنَّا لَمَرْدُودُونَ فِي الْحَافِرَةِ
( 10 ) 
«እኛ ወደ መጀመሪያይቱ ኹነታ ተመላሾች ነን?» ይላሉ፡፡

أَإِذَا كُنَّا عِظَامًا نَّخِرَةً
( 11 ) 
«የበሰበሱ አጥንቶች በኾን ጊዜ (እንቀሰቀሳለን?)»

قَالُوا تِلْكَ إِذًا كَرَّةٌ خَاسِرَةٌ
( 12 ) 
«ይህቺ ያን ጊዜ ባለ ከሳራ መመለስ ናት» ይላሉ፡፡

فَإِنَّمَا هِيَ زَجْرَةٌ وَاحِدَةٌ
( 13 ) 
እርሷም አንዲት ጩኸት ብቻ ናት፡፡

فَإِذَا هُم بِالسَّاهِرَةِ
( 14 ) 
ወዲያውኑም እነርሱ እንቅልፍ በሌለባት (ምድር) ላይ ይኾናሉ፡፡

هَلْ أَتَاكَ حَدِيثُ مُوسَىٰ
( 15 ) 
የሙሳ ወሬ መጣልህን?

إِذْ نَادَاهُ رَبُّهُ بِالْوَادِ الْمُقَدَّسِ طُوًى
( 16 ) 
ጌታው በተቀደሰው ሸለቆ በጡዋ በጠራው ጊዜ፤

اذْهَبْ إِلَىٰ فِرْعَوْنَ إِنَّهُ طَغَىٰ
( 17 ) 
ወደ ፈርዖን ኺድ፡፡ እርሱ ወሰን አልፏልና፡፡

فَقُلْ هَل لَّكَ إِلَىٰ أَن تَزَكَّىٰ
( 18 ) 
በለውም፡- «ወደ መጥራራትህ ላንተ (መንገድ) አለህን?»

وَأَهْدِيَكَ إِلَىٰ رَبِّكَ فَتَخْشَىٰ
( 19 ) 
«ወደ ጌታህም ልመራህ ትፈራውም ዘንድ፤ (መንገድ አለህን?)» አለው፡፡

فَأَرَاهُ الْآيَةَ الْكُبْرَىٰ
( 20 ) 
ታላቂቱንም ተዓምር አሳየው፡፡

فَكَذَّبَ وَعَصَىٰ
( 21 ) 
አስተባበለም፤ አመጸም፡፡

ثُمَّ أَدْبَرَ يَسْعَىٰ
( 22 ) 
ከዚያም (ለማጥፋት) የሚተጋ ኾኖ ዞረ፡፡

فَحَشَرَ فَنَادَىٰ
( 23 ) 
(ሰራዊቶቹን) ሰበሰበም፤ ተጣራም፡፡

فَقَالَ أَنَا رَبُّكُمُ الْأَعْلَىٰ
( 24 ) 
አለም፡- «እኔ ታላቁ ጌታችሁ ነኝ፡፡»

فَأَخَذَهُ اللَّهُ نَكَالَ الْآخِرَةِ وَالْأُولَىٰ
( 25 ) 
አላህም በኋለኛይቱና በፊተኛይቱ (ቃል) ቅጣት ያዘው፡፡

إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَعِبْرَةً لِّمَن يَخْشَىٰ
( 26 ) 
በዚህ ውስጥ ለሚፈራ ሰው በእርግጥ መገምገሚያ አለበት፡፡

أَأَنتُمْ أَشَدُّ خَلْقًا أَمِ السَّمَاءُ ۚ بَنَاهَا
( 27 ) 
ባፈጣጠር እናንተ ይበልጥ የበረታችሁ ናችሁን? ወይንስ ሰማይ? (አላህ) ገነባት፡፡

رَفَعَ سَمْكَهَا فَسَوَّاهَا
( 28 ) 
ከፍታዋን አጓነ፤ አስተካከላትም፡፡

وَأَغْطَشَ لَيْلَهَا وَأَخْرَجَ ضُحَاهَا
( 29 ) 
ሌሊቷንም አጨለመ፡፡ ቀንዋንም ገለጸ፡፡

وَالْأَرْضَ بَعْدَ ذَٰلِكَ دَحَاهَا
( 30 ) 
ምድርንም ከዚህ በኋላ ዘረጋት፡፡

أَخْرَجَ مِنْهَا مَاءَهَا وَمَرْعَاهَا
( 31 ) 
ውሃዋንና ግጦሿን ከእርሷ አወጣ፡፡

وَالْجِبَالَ أَرْسَاهَا
( 32 ) 
ጋራዎችንም አደላደላቸው፡፡

مَتَاعًا لَّكُمْ وَلِأَنْعَامِكُمْ
( 33 ) 
ለእናንተና ለእንስሶቻችሁ መጣቀሚያ ይኾን ዘንድ (ይህን አደረገ)፡፡

فَإِذَا جَاءَتِ الطَّامَّةُ الْكُبْرَىٰ
( 34 ) 
ታላቂቱም መዐት በመጣች ጊዜ፣

يَوْمَ يَتَذَكَّرُ الْإِنسَانُ مَا سَعَىٰ
( 35 ) 
ሰው ሁሉ የሠራውን በሚያስታውስበት ቀን፣

وَبُرِّزَتِ الْجَحِيمُ لِمَن يَرَىٰ
( 36 ) 
ገሀነምም ለሚያይ ሰው በተገለጠች ጊዜ፣

فَأَمَّا مَن طَغَىٰ
( 37 ) 
የካደ ሰውማ፣

وَآثَرَ الْحَيَاةَ الدُّنْيَا
( 38 ) 
ቅርቢቱንም ሕይወት የመረጠ፣

فَإِنَّ الْجَحِيمَ هِيَ الْمَأْوَىٰ
( 39 ) 
ገሀነም እርሷ በእርግጥ መኖሪያው ናት፡፡

وَأَمَّا مَنْ خَافَ مَقَامَ رَبِّهِ وَنَهَى النَّفْسَ عَنِ الْهَوَىٰ
( 40 ) 
በጌታው ፊት መቆምን የፈራ ሰውማ ነፍሱንም ከዝንባሌዋ የከለከለ

فَإِنَّ الْجَنَّةَ هِيَ الْمَأْوَىٰ
( 41 ) 
ገነት እርሷ በእርግጥ መኖሪያው ናት፡፡

يَسْأَلُونَكَ عَنِ السَّاعَةِ أَيَّانَ مُرْسَاهَا
( 42 ) 
«ከሰዓቲቱ መቼ ነው መኾኛዋ?» ሲሉ ይጠይቁሃል፡፡

فِيمَ أَنتَ مِن ذِكْرَاهَا
( 43 ) 
አንተ እርሷን ከማስታወስ በምን ውስጥ ነህ?

إِلَىٰ رَبِّكَ مُنتَهَاهَا
( 44 ) 
(የዕውቀት) መጨረሻዋ ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡

إِنَّمَا أَنتَ مُنذِرُ مَن يَخْشَاهَا
( 45 ) 
አንተ የሚፈራትን ሰው አስፈራሪ ብቻ ነህ፡፡

كَأَنَّهُمْ يَوْمَ يَرَوْنَهَا لَمْ يَلْبَثُوا إِلَّا عَشِيَّةً أَوْ ضُحَاهَا
( 46 ) 
እነርሱ በሚያዩዋት ቀን ያንዲት ቀን ምሽትን ወይም ረፏዷን እንጅ ያልቆዩ ይመስላሉ፡፡
