Surah አል ቀለም

አማርኛ Muhammad Sadiq & Sani Habib

Surah አል ቀለም - Aya count 52
Facebook Twitter Google+ Pinterest Reddit StumbleUpon Linkedin Tumblr Google Bookmarks Email
ن ۚ وَالْقَلَمِ وَمَا يَسْطُرُونَ ( 1 ) አል ቀለም - Aya 1
ነ.(ኑን)፤ በብርእ እምላለሁ በዚያም (መልአኮች) በሚጽፉት፡፡ አል ቀለም - Aya 1
مَا أَنتَ بِنِعْمَةِ رَبِّكَ بِمَجْنُونٍ ( 2 ) አል ቀለም - Aya 2
አንተ በጌታህ ጸጋ የተጎናጸፍክ ስትኾን ዕብድ አይደለህም፡፡ አል ቀለም - Aya 2
وَإِنَّ لَكَ لَأَجْرًا غَيْرَ مَمْنُونٍ ( 3 ) አል ቀለም - Aya 3
ላንተም (ከጌታህ) የማይቋረጥ ዋጋ በእርግጥ አልለህ፡፡ አል ቀለም - Aya 3
وَإِنَّكَ لَعَلَىٰ خُلُقٍ عَظِيمٍ ( 4 ) አል ቀለም - Aya 4
አንተም በታላቅ ጠባይ ላይ ነህ፡፡ አል ቀለም - Aya 4
فَسَتُبْصِرُ وَيُبْصِرُونَ ( 5 ) አል ቀለም - Aya 5
ወደፊትም ታያለህ፤ ያያሉም፡፡ አል ቀለም - Aya 5
بِأَييِّكُمُ الْمَفْتُونُ ( 6 ) አል ቀለም - Aya 6
ዕብደት በማንኛችሁ እንዳልለ፡፡ አል ቀለም - Aya 6
إِنَّ رَبَّكَ هُوَ أَعْلَمُ بِمَن ضَلَّ عَن سَبِيلِهِ وَهُوَ أَعْلَمُ بِالْمُهْتَدِينَ ( 7 ) አል ቀለም - Aya 7
ጌታህ እርሱ ከመንገዱ የተሳሳተውን ሰው ዐዋቂ ነው፡፡ እርሱም ተመሪዎቹን ዐዋቂ ነው፡፡ አል ቀለም - Aya 7
فَلَا تُطِعِ الْمُكَذِّبِينَ ( 8 ) አል ቀለም - Aya 8
ለአስተባባዮችም አትታዝዙ፡፡ አል ቀለም - Aya 8
وَدُّوا لَوْ تُدْهِنُ فَيُدْهِنُونَ ( 9 ) አል ቀለም - Aya 9
ብትመሳሰላቸውና ቢመሳሰሉህ ተመኙ፡፡ አል ቀለም - Aya 9
وَلَا تُطِعْ كُلَّ حَلَّافٍ مَّهِينٍ ( 10 ) አል ቀለም - Aya 10
ወራዳንም ሁሉ አትታዘዝ፡፡ አል ቀለም - Aya 10
هَمَّازٍ مَّشَّاءٍ بِنَمِيمٍ ( 11 ) አል ቀለም - Aya 11
ሰውን አነዋሪንና በማሳበቅ ኼያጅን፡፡ አል ቀለም - Aya 11
مَّنَّاعٍ لِّلْخَيْرِ مُعْتَدٍ أَثِيمٍ ( 12 ) አል ቀለም - Aya 12
ለበጎ ነገር በጣም ከልካይን፣ ወሰን አላፊን፣ ኃጢአተኛን፤ አል ቀለም - Aya 12
عُتُلٍّ بَعْدَ ذَٰلِكَ زَنِيمٍ ( 13 ) አል ቀለም - Aya 13
ልበ ደረቅን፣ ከዚህ በኋላ ዲቃላን (ሁሉ አትታዘዝ)፡፡ አል ቀለም - Aya 13
أَن كَانَ ذَا مَالٍ وَبَنِينَ ( 14 ) አል ቀለም - Aya 14
የገንዘብና የልጆች ባለቤት በመኾኑ (ያስተባብላል)፡፡ አል ቀለም - Aya 14
إِذَا تُتْلَىٰ عَلَيْهِ آيَاتُنَا قَالَ أَسَاطِيرُ الْأَوَّلِينَ ( 15 ) አል ቀለም - Aya 15
በእርሱ ላይ አንቀጾቻችን በሚነበቡ ጊዜ «የመጀመሪያዎቹ ሰዎች ተረቶች ናቸው» ይላል፡፡ አል ቀለም - Aya 15
سَنَسِمُهُ عَلَى الْخُرْطُومِ ( 16 ) አል ቀለም - Aya 16
በአፍንጫው ላይ በእርግጥ (የሚነወርበት) ምልክት እናደርግበታለን፡፡ አል ቀለም - Aya 16
إِنَّا بَلَوْنَاهُمْ كَمَا بَلَوْنَا أَصْحَابَ الْجَنَّةِ إِذْ أَقْسَمُوا لَيَصْرِمُنَّهَا مُصْبِحِينَ ( 17 ) አል ቀለም - Aya 17
እኛ የአትክልቲቱን ባለቤቶቸ እንደ ሞከርን (የመካን ሰዎች) ሞከርናቸው፡፡ ማልደው (ፍሬዋን) ሊለቅሟት በማሉ ጊዜ፡፡ አል ቀለም - Aya 17
وَلَا يَسْتَثْنُونَ ( 18 ) አል ቀለም - Aya 18
(በመሓላቸው) አያስቀሩምም፡፡ አል ቀለም - Aya 18
فَطَافَ عَلَيْهَا طَائِفٌ مِّن رَّبِّكَ وَهُمْ نَائِمُونَ ( 19 ) አል ቀለም - Aya 19
እነርሱ የተኙ ኾነውም ሳሉ ከጌታህ የኾነ ዟሪ በእርሷ ላይ ዞረባት፡፡ አል ቀለም - Aya 19
فَأَصْبَحَتْ كَالصَّرِيمِ ( 20 ) አል ቀለም - Aya 20
እንደ ሌሊት ጨለማም ኾና አነጋች፤ (ከሰለች)፡፡ አል ቀለም - Aya 20
فَتَنَادَوْا مُصْبِحِينَ ( 21 ) አል ቀለም - Aya 21
ያነጉም ኾነው ተጠራሩ፡፡ አል ቀለም - Aya 21
أَنِ اغْدُوا عَلَىٰ حَرْثِكُمْ إِن كُنتُمْ صَارِمِينَ ( 22 ) አል ቀለም - Aya 22
«ቆራጮች እንደ ኾናችሁ በእርሻቸሁ ላይ ማልዱ» በማለት፡፡ አል ቀለም - Aya 22
فَانطَلَقُوا وَهُمْ يَتَخَافَتُونَ ( 23 ) አል ቀለም - Aya 23
እነርሱ የሚንሾካሾኩ ኾነው ኼዱም፡፡ አል ቀለም - Aya 23
أَن لَّا يَدْخُلَنَّهَا الْيَوْمَ عَلَيْكُم مِّسْكِينٌ ( 24 ) አል ቀለም - Aya 24
ዛሬ በእናንተ ላይ ድኻ እንዳይገባት በማለት፡፡ አል ቀለም - Aya 24
وَغَدَوْا عَلَىٰ حَرْدٍ قَادِرِينَ ( 25 ) አል ቀለም - Aya 25
(ድኾችን) በመከልከልም ላይ (በሐሳባቸው) ቻዮች ኾነው ማለዱ፡፡ አል ቀለም - Aya 25
فَلَمَّا رَأَوْهَا قَالُوا إِنَّا لَضَالُّونَ ( 26 ) አል ቀለም - Aya 26
(ተቃጥላ) ባዩዋትም ጊዜ «እኛ በእርግጥ ተሳሳቾች ነን» አሉ፡፡ አል ቀለም - Aya 26
بَلْ نَحْنُ مَحْرُومُونَ ( 27 ) አል ቀለም - Aya 27
«ይልቁንም እኛ የተከለከልን ነን» አሉ፡፡ አል ቀለም - Aya 27
قَالَ أَوْسَطُهُمْ أَلَمْ أَقُل لَّكُمْ لَوْلَا تُسَبِّحُونَ ( 28 ) አል ቀለም - Aya 28
ትክክለኛቸው «ለእናንተ አላህን ለምን አታጠሩም አላልኳችሁምን?» አላቸው፡፡ አል ቀለም - Aya 28
قَالُوا سُبْحَانَ رَبِّنَا إِنَّا كُنَّا ظَالِمِينَ ( 29 ) አል ቀለም - Aya 29
«ጌታችን ጥራት ይገባው፡፡ እኛ በዳዮች ነበርን፤» አሉ፡፡ አል ቀለም - Aya 29
فَأَقْبَلَ بَعْضُهُمْ عَلَىٰ بَعْضٍ يَتَلَاوَمُونَ ( 30 ) አል ቀለም - Aya 30
የሚወቃቀሱም ኾነው ከፊሎቻቸው በከፊሉ ላይ መጡ፡፡ አል ቀለም - Aya 30
قَالُوا يَا وَيْلَنَا إِنَّا كُنَّا طَاغِينَ ( 31 ) አል ቀለም - Aya 31
«ዋ ጥፋታችን! እኛ ድንበር አላፊዎች ነበርን፤» አሉ፡፡ አል ቀለም - Aya 31
عَسَىٰ رَبُّنَا أَن يُبْدِلَنَا خَيْرًا مِّنْهَا إِنَّا إِلَىٰ رَبِّنَا رَاغِبُونَ ( 32 ) አል ቀለም - Aya 32
«ጌታችን ከእርሷ የተሻለን (አትክልት) ሊለውጠን ይከጀላል፡፡ እኛ ወደ ጌታችን ከጃዮች ነን፤» (አሉ)፡፡ አል ቀለም - Aya 32
كَذَٰلِكَ الْعَذَابُ ۖ وَلَعَذَابُ الْآخِرَةِ أَكْبَرُ ۚ لَوْ كَانُوا يَعْلَمُونَ ( 33 ) አል ቀለም - Aya 33
ቅጣቱ እንደዚሁ ነው፡፡ የመጨረሻይቱም ዓለም ቅጣት ታላቅ ነው፡፡ የሚያውቁት በኾኑ ኖሮ (በተጠነቀቁ ነበር)፡፡ አል ቀለም - Aya 33
إِنَّ لِلْمُتَّقِينَ عِندَ رَبِّهِمْ جَنَّاتِ النَّعِيمِ ( 34 ) አል ቀለም - Aya 34
ለጥንቁቆቹ በጌታቸው ዘንድ መጠቀሚያ ገነቶች አሏቸው፡፡ አል ቀለም - Aya 34
أَفَنَجْعَلُ الْمُسْلِمِينَ كَالْمُجْرِمِينَ ( 35 ) አል ቀለም - Aya 35
ሙስሊሞቹን እንደ ከሓዲዎች እናደርጋለን? አል ቀለም - Aya 35
مَا لَكُمْ كَيْفَ تَحْكُمُونَ ( 36 ) አል ቀለም - Aya 36
ለእናንተ ምን (አስረጅ) አላችሁ? እንዴት ትፈርዳላችሁ፡፡ አል ቀለም - Aya 36
أَمْ لَكُمْ كِتَابٌ فِيهِ تَدْرُسُونَ ( 37 ) አል ቀለም - Aya 37
በእውነቱ ለእናንተ በእርሱ የምታጠኑበት መጽሐፍ አላችሁን? አል ቀለም - Aya 37
إِنَّ لَكُمْ فِيهِ لَمَا تَخَيَّرُونَ ( 38 ) አል ቀለም - Aya 38
በውስጡ ለእናንተ የምትመርጡት አላችሁ (የሚል) አል ቀለም - Aya 38
أَمْ لَكُمْ أَيْمَانٌ عَلَيْنَا بَالِغَةٌ إِلَىٰ يَوْمِ الْقِيَامَةِ ۙ إِنَّ لَكُمْ لَمَا تَحْكُمُونَ ( 39 ) አል ቀለም - Aya 39
ወይስ ለእናንተ የምትፈርዱት አላችሁ በማለት (ቃል ኪዳን የገባንላችሁ) እስከ ትንሣኤ ቀን ደራሽ የኾኑ መሓላዎች ለእናንተ በእኛ ላይ አሏችሁን? አል ቀለም - Aya 39
سَلْهُمْ أَيُّهُم بِذَٰلِكَ زَعِيمٌ ( 40 ) አል ቀለም - Aya 40
በዚህ ማንኛቸው ተያያዥ እንደ ኾነ ጠይቃቸው፡፡ አል ቀለም - Aya 40
أَمْ لَهُمْ شُرَكَاءُ فَلْيَأْتُوا بِشُرَكَائِهِمْ إِن كَانُوا صَادِقِينَ ( 41 ) አል ቀለም - Aya 41
ወይስ ለእነርሱ (በፍርዳቸው ተስማሚ) «ተጋሪዎች» አሏቸውን? እውነተኞችም እንደኾኑ «ተጋሪዎቻቸውን» ያምጡ፡፡ አል ቀለም - Aya 41
يَوْمَ يُكْشَفُ عَن سَاقٍ وَيُدْعَوْنَ إِلَى السُّجُودِ فَلَا يَسْتَطِيعُونَ ( 42 ) አል ቀለም - Aya 42
ባት የሚገለጥበትን (ከሓዲዎች) ወደ መስገድም የሚጥጠሩበትንና የማይችሉበት ቀን (አስታውስ)፡፡ አል ቀለም - Aya 42
خَاشِعَةً أَبْصَارُهُمْ تَرْهَقُهُمْ ذِلَّةٌ ۖ وَقَدْ كَانُوا يُدْعَوْنَ إِلَى السُّجُودِ وَهُمْ سَالِمُونَ ( 43 ) አል ቀለም - Aya 43
ዓይኖቻቸው የፈሩ ውርደት የምትሸፍናቸው ሲኾኑ፤ (ወደ ስግደት የሚጠሩበትን)፤ እነርሱም (በምድረ ዓለም) ደህና ኾነው ሳሉ ወደ ስግደት በእርግጥ ይጠሩ ነበሩ፡፡ አል ቀለም - Aya 43
فَذَرْنِي وَمَن يُكَذِّبُ بِهَٰذَا الْحَدِيثِ ۖ سَنَسْتَدْرِجُهُم مِّنْ حَيْثُ لَا يَعْلَمُونَ ( 44 ) አል ቀለም - Aya 44
በዚህም ንግግር ከሚያስተባብሉት ሰዎች ጋር ተዎኝ፡፡ (እነርሱን እኔ እበቃሃለሁ)፡፡ ከማያውቁት ስፍራ አዘናግተን እንይዛቸዋለን፡፡ አል ቀለም - Aya 44
وَأُمْلِي لَهُمْ ۚ إِنَّ كَيْدِي مَتِينٌ ( 45 ) አል ቀለም - Aya 45
እነርሱንም አዘገያለሁ፡፡ ዘዴዬ ብርቱ ነውና፡፡ አል ቀለም - Aya 45
أَمْ تَسْأَلُهُمْ أَجْرًا فَهُم مِّن مَّغْرَمٍ مُّثْقَلُونَ ( 46 ) አል ቀለም - Aya 46
በእውነቱ ዋጋን ትጠይቃቸዋለህን? ስለዚህ እነርሱ ከዕዳ የተከበዱ ናቸውን? አል ቀለም - Aya 46
أَمْ عِندَهُمُ الْغَيْبُ فَهُمْ يَكْتُبُونَ ( 47 ) አል ቀለም - Aya 47
ወይስ እነርሱ ዘንድ የሩቁ ምስጢር ዕውቀት አልለን? ስለዚህ እነርሱ ይጽፋሉን? አል ቀለም - Aya 47
فَاصْبِرْ لِحُكْمِ رَبِّكَ وَلَا تَكُن كَصَاحِبِ الْحُوتِ إِذْ نَادَىٰ وَهُوَ مَكْظُومٌ ( 48 ) አል ቀለም - Aya 48
ለጌታህም ፍርድ ታገሥ፤ (በመበሳጨትና ባለ መታገሥ) እንደ ዓሣው ባለቤትም (እንደ ዮናስ) አትኹን፡፡ እርሱ በጭንቀት የተመላ ኾኖ (ጌታውን) በተጣራ ጊዜ፡፡ አል ቀለም - Aya 48
لَّوْلَا أَن تَدَارَكَهُ نِعْمَةٌ مِّن رَّبِّهِ لَنُبِذَ بِالْعَرَاءِ وَهُوَ مَذْمُومٌ ( 49 ) አል ቀለም - Aya 49
ከጌታው የኾነ ጸጋ ባላገኘው ኖሮ በምድረ በዳ ተወቃሽ ኾኖ በተጣለ ነበር፡፡ አል ቀለም - Aya 49
فَاجْتَبَاهُ رَبُّهُ فَجَعَلَهُ مِنَ الصَّالِحِينَ ( 50 ) አል ቀለም - Aya 50
ጌታውም (በነቢይነት) መረጠው፡፡ ከደጋጎቹም አደረገው፡፡ አል ቀለም - Aya 50
وَإِن يَكَادُ الَّذِينَ كَفَرُوا لَيُزْلِقُونَكَ بِأَبْصَارِهِمْ لَمَّا سَمِعُوا الذِّكْرَ وَيَقُولُونَ إِنَّهُ لَمَجْنُونٌ ( 51 ) አል ቀለም - Aya 51
እነሆ እነዚያም የካዱት ሰዎች ቁርኣኑን በሰሙ ጊዜ በዓይኖቻቸው ሊጥሉህ (ሊያጠፉህ) ይቀርባሉ፡፡ «እርሱም በእርግጥ ዕብድ ነው» ይላሉ፡፡ አል ቀለም - Aya 51
وَمَا هُوَ إِلَّا ذِكْرٌ لِّلْعَالَمِينَ ( 52 ) አል ቀለም - Aya 52
ግን እርሱ (ቁርኣን) ለዓለማት መገሰጫ እንጂ ሌላ አይደለም፡፡ አል ቀለም - Aya 52
Facebook Twitter Google+ Pinterest Reddit StumbleUpon Linkedin Tumblr Google Bookmarks Email

Select Translation

Select surah