አማርኛ Muhammad Sadiq & Sani Habib
Surah አል ቀለም - Aya count 52
ن ۚ وَالْقَلَمِ وَمَا يَسْطُرُونَ
( 1 ) 
ነ.(ኑን)፤ በብርእ እምላለሁ በዚያም (መልአኮች) በሚጽፉት፡፡

مَا أَنتَ بِنِعْمَةِ رَبِّكَ بِمَجْنُونٍ
( 2 ) 
አንተ በጌታህ ጸጋ የተጎናጸፍክ ስትኾን ዕብድ አይደለህም፡፡

وَإِنَّ لَكَ لَأَجْرًا غَيْرَ مَمْنُونٍ
( 3 ) 
ላንተም (ከጌታህ) የማይቋረጥ ዋጋ በእርግጥ አልለህ፡፡

وَإِنَّكَ لَعَلَىٰ خُلُقٍ عَظِيمٍ
( 4 ) 
አንተም በታላቅ ጠባይ ላይ ነህ፡፡

فَسَتُبْصِرُ وَيُبْصِرُونَ
( 5 ) 
ወደፊትም ታያለህ፤ ያያሉም፡፡

بِأَييِّكُمُ الْمَفْتُونُ
( 6 ) 
ዕብደት በማንኛችሁ እንዳልለ፡፡

إِنَّ رَبَّكَ هُوَ أَعْلَمُ بِمَن ضَلَّ عَن سَبِيلِهِ وَهُوَ أَعْلَمُ بِالْمُهْتَدِينَ
( 7 ) 
ጌታህ እርሱ ከመንገዱ የተሳሳተውን ሰው ዐዋቂ ነው፡፡ እርሱም ተመሪዎቹን ዐዋቂ ነው፡፡

فَلَا تُطِعِ الْمُكَذِّبِينَ
( 8 ) 
ለአስተባባዮችም አትታዝዙ፡፡

وَدُّوا لَوْ تُدْهِنُ فَيُدْهِنُونَ
( 9 ) 
ብትመሳሰላቸውና ቢመሳሰሉህ ተመኙ፡፡

وَلَا تُطِعْ كُلَّ حَلَّافٍ مَّهِينٍ
( 10 ) 
ወራዳንም ሁሉ አትታዘዝ፡፡

هَمَّازٍ مَّشَّاءٍ بِنَمِيمٍ
( 11 ) 
ሰውን አነዋሪንና በማሳበቅ ኼያጅን፡፡

مَّنَّاعٍ لِّلْخَيْرِ مُعْتَدٍ أَثِيمٍ
( 12 ) 
ለበጎ ነገር በጣም ከልካይን፣ ወሰን አላፊን፣ ኃጢአተኛን፤

عُتُلٍّ بَعْدَ ذَٰلِكَ زَنِيمٍ
( 13 ) 
ልበ ደረቅን፣ ከዚህ በኋላ ዲቃላን (ሁሉ አትታዘዝ)፡፡

أَن كَانَ ذَا مَالٍ وَبَنِينَ
( 14 ) 
የገንዘብና የልጆች ባለቤት በመኾኑ (ያስተባብላል)፡፡

إِذَا تُتْلَىٰ عَلَيْهِ آيَاتُنَا قَالَ أَسَاطِيرُ الْأَوَّلِينَ
( 15 ) 
በእርሱ ላይ አንቀጾቻችን በሚነበቡ ጊዜ «የመጀመሪያዎቹ ሰዎች ተረቶች ናቸው» ይላል፡፡

سَنَسِمُهُ عَلَى الْخُرْطُومِ
( 16 ) 
በአፍንጫው ላይ በእርግጥ (የሚነወርበት) ምልክት እናደርግበታለን፡፡

إِنَّا بَلَوْنَاهُمْ كَمَا بَلَوْنَا أَصْحَابَ الْجَنَّةِ إِذْ أَقْسَمُوا لَيَصْرِمُنَّهَا مُصْبِحِينَ
( 17 ) 
እኛ የአትክልቲቱን ባለቤቶቸ እንደ ሞከርን (የመካን ሰዎች) ሞከርናቸው፡፡ ማልደው (ፍሬዋን) ሊለቅሟት በማሉ ጊዜ፡፡

وَلَا يَسْتَثْنُونَ
( 18 ) 
(በመሓላቸው) አያስቀሩምም፡፡

فَطَافَ عَلَيْهَا طَائِفٌ مِّن رَّبِّكَ وَهُمْ نَائِمُونَ
( 19 ) 
እነርሱ የተኙ ኾነውም ሳሉ ከጌታህ የኾነ ዟሪ በእርሷ ላይ ዞረባት፡፡

فَأَصْبَحَتْ كَالصَّرِيمِ
( 20 ) 
እንደ ሌሊት ጨለማም ኾና አነጋች፤ (ከሰለች)፡፡

فَتَنَادَوْا مُصْبِحِينَ
( 21 ) 
ያነጉም ኾነው ተጠራሩ፡፡

أَنِ اغْدُوا عَلَىٰ حَرْثِكُمْ إِن كُنتُمْ صَارِمِينَ
( 22 ) 
«ቆራጮች እንደ ኾናችሁ በእርሻቸሁ ላይ ማልዱ» በማለት፡፡

فَانطَلَقُوا وَهُمْ يَتَخَافَتُونَ
( 23 ) 
እነርሱ የሚንሾካሾኩ ኾነው ኼዱም፡፡

أَن لَّا يَدْخُلَنَّهَا الْيَوْمَ عَلَيْكُم مِّسْكِينٌ
( 24 ) 
ዛሬ በእናንተ ላይ ድኻ እንዳይገባት በማለት፡፡

وَغَدَوْا عَلَىٰ حَرْدٍ قَادِرِينَ
( 25 ) 
(ድኾችን) በመከልከልም ላይ (በሐሳባቸው) ቻዮች ኾነው ማለዱ፡፡

فَلَمَّا رَأَوْهَا قَالُوا إِنَّا لَضَالُّونَ
( 26 ) 
(ተቃጥላ) ባዩዋትም ጊዜ «እኛ በእርግጥ ተሳሳቾች ነን» አሉ፡፡

بَلْ نَحْنُ مَحْرُومُونَ
( 27 ) 
«ይልቁንም እኛ የተከለከልን ነን» አሉ፡፡

قَالَ أَوْسَطُهُمْ أَلَمْ أَقُل لَّكُمْ لَوْلَا تُسَبِّحُونَ
( 28 ) 
ትክክለኛቸው «ለእናንተ አላህን ለምን አታጠሩም አላልኳችሁምን?» አላቸው፡፡

قَالُوا سُبْحَانَ رَبِّنَا إِنَّا كُنَّا ظَالِمِينَ
( 29 ) 
«ጌታችን ጥራት ይገባው፡፡ እኛ በዳዮች ነበርን፤» አሉ፡፡

فَأَقْبَلَ بَعْضُهُمْ عَلَىٰ بَعْضٍ يَتَلَاوَمُونَ
( 30 ) 
የሚወቃቀሱም ኾነው ከፊሎቻቸው በከፊሉ ላይ መጡ፡፡

قَالُوا يَا وَيْلَنَا إِنَّا كُنَّا طَاغِينَ
( 31 ) 
«ዋ ጥፋታችን! እኛ ድንበር አላፊዎች ነበርን፤» አሉ፡፡

عَسَىٰ رَبُّنَا أَن يُبْدِلَنَا خَيْرًا مِّنْهَا إِنَّا إِلَىٰ رَبِّنَا رَاغِبُونَ
( 32 ) 
«ጌታችን ከእርሷ የተሻለን (አትክልት) ሊለውጠን ይከጀላል፡፡ እኛ ወደ ጌታችን ከጃዮች ነን፤» (አሉ)፡፡

كَذَٰلِكَ الْعَذَابُ ۖ وَلَعَذَابُ الْآخِرَةِ أَكْبَرُ ۚ لَوْ كَانُوا يَعْلَمُونَ
( 33 ) 
ቅጣቱ እንደዚሁ ነው፡፡ የመጨረሻይቱም ዓለም ቅጣት ታላቅ ነው፡፡ የሚያውቁት በኾኑ ኖሮ (በተጠነቀቁ ነበር)፡፡

إِنَّ لِلْمُتَّقِينَ عِندَ رَبِّهِمْ جَنَّاتِ النَّعِيمِ
( 34 ) 
ለጥንቁቆቹ በጌታቸው ዘንድ መጠቀሚያ ገነቶች አሏቸው፡፡

أَفَنَجْعَلُ الْمُسْلِمِينَ كَالْمُجْرِمِينَ
( 35 ) 
ሙስሊሞቹን እንደ ከሓዲዎች እናደርጋለን?

مَا لَكُمْ كَيْفَ تَحْكُمُونَ
( 36 ) 
ለእናንተ ምን (አስረጅ) አላችሁ? እንዴት ትፈርዳላችሁ፡፡

أَمْ لَكُمْ كِتَابٌ فِيهِ تَدْرُسُونَ
( 37 ) 
በእውነቱ ለእናንተ በእርሱ የምታጠኑበት መጽሐፍ አላችሁን?

إِنَّ لَكُمْ فِيهِ لَمَا تَخَيَّرُونَ
( 38 ) 
በውስጡ ለእናንተ የምትመርጡት አላችሁ (የሚል)

أَمْ لَكُمْ أَيْمَانٌ عَلَيْنَا بَالِغَةٌ إِلَىٰ يَوْمِ الْقِيَامَةِ ۙ إِنَّ لَكُمْ لَمَا تَحْكُمُونَ
( 39 ) 
ወይስ ለእናንተ የምትፈርዱት አላችሁ በማለት (ቃል ኪዳን የገባንላችሁ) እስከ ትንሣኤ ቀን ደራሽ የኾኑ መሓላዎች ለእናንተ በእኛ ላይ አሏችሁን?

سَلْهُمْ أَيُّهُم بِذَٰلِكَ زَعِيمٌ
( 40 ) 
በዚህ ማንኛቸው ተያያዥ እንደ ኾነ ጠይቃቸው፡፡

أَمْ لَهُمْ شُرَكَاءُ فَلْيَأْتُوا بِشُرَكَائِهِمْ إِن كَانُوا صَادِقِينَ
( 41 ) 
ወይስ ለእነርሱ (በፍርዳቸው ተስማሚ) «ተጋሪዎች» አሏቸውን? እውነተኞችም እንደኾኑ «ተጋሪዎቻቸውን» ያምጡ፡፡

يَوْمَ يُكْشَفُ عَن سَاقٍ وَيُدْعَوْنَ إِلَى السُّجُودِ فَلَا يَسْتَطِيعُونَ
( 42 ) 
ባት የሚገለጥበትን (ከሓዲዎች) ወደ መስገድም የሚጥጠሩበትንና የማይችሉበት ቀን (አስታውስ)፡፡

خَاشِعَةً أَبْصَارُهُمْ تَرْهَقُهُمْ ذِلَّةٌ ۖ وَقَدْ كَانُوا يُدْعَوْنَ إِلَى السُّجُودِ وَهُمْ سَالِمُونَ
( 43 ) 
ዓይኖቻቸው የፈሩ ውርደት የምትሸፍናቸው ሲኾኑ፤ (ወደ ስግደት የሚጠሩበትን)፤ እነርሱም (በምድረ ዓለም) ደህና ኾነው ሳሉ ወደ ስግደት በእርግጥ ይጠሩ ነበሩ፡፡

فَذَرْنِي وَمَن يُكَذِّبُ بِهَٰذَا الْحَدِيثِ ۖ سَنَسْتَدْرِجُهُم مِّنْ حَيْثُ لَا يَعْلَمُونَ
( 44 ) 
በዚህም ንግግር ከሚያስተባብሉት ሰዎች ጋር ተዎኝ፡፡ (እነርሱን እኔ እበቃሃለሁ)፡፡ ከማያውቁት ስፍራ አዘናግተን እንይዛቸዋለን፡፡

وَأُمْلِي لَهُمْ ۚ إِنَّ كَيْدِي مَتِينٌ
( 45 ) 
እነርሱንም አዘገያለሁ፡፡ ዘዴዬ ብርቱ ነውና፡፡

أَمْ تَسْأَلُهُمْ أَجْرًا فَهُم مِّن مَّغْرَمٍ مُّثْقَلُونَ
( 46 ) 
በእውነቱ ዋጋን ትጠይቃቸዋለህን? ስለዚህ እነርሱ ከዕዳ የተከበዱ ናቸውን?

أَمْ عِندَهُمُ الْغَيْبُ فَهُمْ يَكْتُبُونَ
( 47 ) 
ወይስ እነርሱ ዘንድ የሩቁ ምስጢር ዕውቀት አልለን? ስለዚህ እነርሱ ይጽፋሉን?

فَاصْبِرْ لِحُكْمِ رَبِّكَ وَلَا تَكُن كَصَاحِبِ الْحُوتِ إِذْ نَادَىٰ وَهُوَ مَكْظُومٌ
( 48 ) 
ለጌታህም ፍርድ ታገሥ፤ (በመበሳጨትና ባለ መታገሥ) እንደ ዓሣው ባለቤትም (እንደ ዮናስ) አትኹን፡፡ እርሱ በጭንቀት የተመላ ኾኖ (ጌታውን) በተጣራ ጊዜ፡፡

لَّوْلَا أَن تَدَارَكَهُ نِعْمَةٌ مِّن رَّبِّهِ لَنُبِذَ بِالْعَرَاءِ وَهُوَ مَذْمُومٌ
( 49 ) 
ከጌታው የኾነ ጸጋ ባላገኘው ኖሮ በምድረ በዳ ተወቃሽ ኾኖ በተጣለ ነበር፡፡

فَاجْتَبَاهُ رَبُّهُ فَجَعَلَهُ مِنَ الصَّالِحِينَ
( 50 ) 
ጌታውም (በነቢይነት) መረጠው፡፡ ከደጋጎቹም አደረገው፡፡

وَإِن يَكَادُ الَّذِينَ كَفَرُوا لَيُزْلِقُونَكَ بِأَبْصَارِهِمْ لَمَّا سَمِعُوا الذِّكْرَ وَيَقُولُونَ إِنَّهُ لَمَجْنُونٌ
( 51 ) 
እነሆ እነዚያም የካዱት ሰዎች ቁርኣኑን በሰሙ ጊዜ በዓይኖቻቸው ሊጥሉህ (ሊያጠፉህ) ይቀርባሉ፡፡ «እርሱም በእርግጥ ዕብድ ነው» ይላሉ፡፡

وَمَا هُوَ إِلَّا ذِكْرٌ لِّلْعَالَمِينَ
( 52 ) 
ግን እርሱ (ቁርኣን) ለዓለማት መገሰጫ እንጂ ሌላ አይደለም፡፡
