አማርኛ Muhammad Sadiq & Sani Habib
Surah አል ሙጠፊፉን - Aya count 36
وَيْلٌ لِّلْمُطَفِّفِينَ
( 1 ) 
ለሰላቢዎች ወዮላቸው፡፡

الَّذِينَ إِذَا اكْتَالُوا عَلَى النَّاسِ يَسْتَوْفُونَ
( 2 ) 
ለእነዚያ ከሰዎች ባስሰፈሩ ጊዜ የሚያስሞሉ፡፡

وَإِذَا كَالُوهُمْ أَو وَّزَنُوهُمْ يُخْسِرُونَ
( 3 ) 
ለእነርሱም (ለሰዎቹ) በሰፈሩ ወይም በመዘኑላቸው ጊዜ የሚያጎድሉ (ለኾኑት)፡፡

أَلَا يَظُنُّ أُولَٰئِكَ أَنَّهُم مَّبْعُوثُونَ
( 4 ) 
እነዚያ እነርሱ ተቀስቃሾች መኾናቸውን አያውቁምን?

لِيَوْمٍ عَظِيمٍ
( 5 ) 
በታላቁ ቀን፡፡

يَوْمَ يَقُومُ النَّاسُ لِرَبِّ الْعَالَمِينَ
( 6 ) 
ሰዎች ሁሉ ለዓለማት ጌታ (ፍርድ)፤ በሚቆሙበት ቀን (ተቀስቃሾች መኾናቸውን)፡፡

كَلَّا إِنَّ كِتَابَ الْفُجَّارِ لَفِي سِجِّينٍ
( 7 ) 
በእውነት የከሓዲዎቹ (የሰላቢዎቹ) መጽሐፍ በእርግጥ በሲጂን ውስጥ ነው፡፡

وَمَا أَدْرَاكَ مَا سِجِّينٌ
( 8 ) 
ሲጂንም ምን እንደ ኾነ ምን አሳወቀህ?

كِتَابٌ مَّرْقُومٌ
( 9 ) 
የታተመ መጽሐፍ ነው፡፡

وَيْلٌ يَوْمَئِذٍ لِّلْمُكَذِّبِينَ
( 10 ) 
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

الَّذِينَ يُكَذِّبُونَ بِيَوْمِ الدِّينِ
( 11 ) 
ለእነዚያ በፍርዱ ቀን ለሚያስተባብሉት፡፡

وَمَا يُكَذِّبُ بِهِ إِلَّا كُلُّ مُعْتَدٍ أَثِيمٍ
( 12 ) 
በእርሱም ወሰን አላፊ ኀጢአተኛ ሁሉ እንጅ ሌላ አያስተባብልም፡፡

إِذَا تُتْلَىٰ عَلَيْهِ آيَاتُنَا قَالَ أَسَاطِيرُ الْأَوَّلِينَ
( 13 ) 
አንቀጾቻችን በእርሱ ላይ በተነበቡ ጊዜ «የመጀመሪያዎቹ ሰዎች ተረቶች ናቸው» ይላል፡፡

كَلَّا ۖ بَلْ ۜ رَانَ عَلَىٰ قُلُوبِهِم مَّا كَانُوا يَكْسِبُونَ
( 14 ) 
ይከልከል፤ ይልቁንም በልቦቻቸው ላይ ይሠሩት የነበሩት (ኀጢአት) ደገደገባቸው፡፡

كَلَّا إِنَّهُمْ عَن رَّبِّهِمْ يَوْمَئِذٍ لَّمَحْجُوبُونَ
( 15 ) 
ይከልከሉ፤ እነርሱ በዚያ ቀን ከጌታቸው (ማየት) ተጋራጆች ናቸው፡፡

ثُمَّ إِنَّهُمْ لَصَالُو الْجَحِيمِ
( 16 ) 
ከዚያም እነርሱ በእርግጥ ገሀነምን ገቢዎች ናቸው፡፡

ثُمَّ يُقَالُ هَٰذَا الَّذِي كُنتُم بِهِ تُكَذِّبُونَ
( 17 ) 
ከዚያም «ይህ ያ በእርሱ ታስተባብሉበት የነበራችሁት ነው» ይባላሉ፡፡

كَلَّا إِنَّ كِتَابَ الْأَبْرَارِ لَفِي عِلِّيِّينَ
( 18 ) 
በእውነቱ የእውነተኞቹ ምእምናን መጽሐፍ በዒሊዮን ውስጥ ነው፡፡

وَمَا أَدْرَاكَ مَا عِلِّيُّونَ
( 19 ) 
ዒሊዮንም ምን እንደ ኾነ ምን አሳወቀህ?

كِتَابٌ مَّرْقُومٌ
( 20 ) 
የታተመ መጽሐፍ ነው፡፡

يَشْهَدُهُ الْمُقَرَّبُونَ
( 21 ) 
ባለሟልዎቹ ይጣዱታል፡፡

إِنَّ الْأَبْرَارَ لَفِي نَعِيمٍ
( 22 ) 
እውነተኞቹ ምእምናን በእርግጥ በድሎት (ገነት) ውስጥ ናቸው፡፡

عَلَى الْأَرَائِكِ يَنظُرُونَ
( 23 ) 
በባለ አጎበር አልጋዎች ላይ ኾነው ይመለከታሉ፡፡

تَعْرِفُ فِي وُجُوهِهِمْ نَضْرَةَ النَّعِيمِ
( 24 ) 
በፊቶቻቸው ላይ የድሎትን ውበት ታውቃለህ፡፡

يُسْقَوْنَ مِن رَّحِيقٍ مَّخْتُومٍ
( 25 ) 
ተጣርቶ ከታተመ ጠጅ ይጠጣሉ፡፡

خِتَامُهُ مِسْكٌ ۚ وَفِي ذَٰلِكَ فَلْيَتَنَافَسِ الْمُتَنَافِسُونَ
( 26 ) 
ማተሚያው ምስክ ከኾነ፤ በዚህም ተሽቀዳዳሚዎች ይሽቀዳደሙ፡፡

وَمِزَاجُهُ مِن تَسْنِيمٍ
( 27 ) 
መበረዣውም ከተስኒም ነው፡፡

عَيْنًا يَشْرَبُ بِهَا الْمُقَرَّبُونَ
( 28 ) 
ባለሟሎቹ ከእርሷ የሚጠጡላት ምንጭ ናት፡፡

إِنَّ الَّذِينَ أَجْرَمُوا كَانُوا مِنَ الَّذِينَ آمَنُوا يَضْحَكُونَ
( 29 ) 
እነዚያ ያምመጹት በእነዚያ ባመኑት በእርግጥ ይስቁ ነበሩ፡፡

وَإِذَا مَرُّوا بِهِمْ يَتَغَامَزُونَ
( 30 ) 
በእነርሱም ላይ ባለፉ ጊዜ ይጠቃቀሱ ነበር፡፡

وَإِذَا انقَلَبُوا إِلَىٰ أَهْلِهِمُ انقَلَبُوا فَكِهِينَ
( 31 ) 
ወደ ቤተሰቦቻቸውም በተመለሱ ጊዜ (በመሳለቃቸው) ተደሳቾች ኾነው ይመለሱ ነበር፡፡

وَإِذَا رَأَوْهُمْ قَالُوا إِنَّ هَٰؤُلَاءِ لَضَالُّونَ
( 32 ) 
ባዩዋቸውም ጊዜ «እነዚህ በእርግጥ ተሳሳቾች ናቸው» ይሉ ነበር፡፡

وَمَا أُرْسِلُوا عَلَيْهِمْ حَافِظِينَ
( 33 ) 
በነርሱ ላይ ተጠባባቂዎች ተደርገው ያልተላኩ ሲኾኑ፡፡

فَالْيَوْمَ الَّذِينَ آمَنُوا مِنَ الْكُفَّارِ يَضْحَكُونَ
( 34 ) 
ዛሬ (በትንሣኤ ቀን) እነዚያ ያመኑት በከሓዲዎቹ ይስቃሉ፡፡

عَلَى الْأَرَائِكِ يَنظُرُونَ
( 35 ) 
በባለ አጎበር አልጋዎች ላይ ኾነው የሚመለከቱ ሲኾኑ (ይስቃሉ)፡፡

هَلْ ثُوِّبَ الْكُفَّارُ مَا كَانُوا يَفْعَلُونَ
( 36 ) 
ከሓዲዎች ይሠሩት የነበሩትን (ዋጋ) ተመነዱን? (ይላሉ)፡፡
